Tuesday, June 30, 2015

ግብረሰዶማዊነት – የማይረባ አዕምሮ ውጤት #1

ዲቮሽ 293/07፥ ማክሰኞ፥ ሰኔ 23/07 ዓ/ም
(በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)
ግብረሰዶማዊነት – የማይረባ አዕምሮ ውጤት #1
እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው (ሮሜ 1፡28)
ከሣምንታት በፊት አየርላንድ 62% በሆነ ሕዝበ ውሳኔ ግብረሰዶማዊነት የሀገሯ ሕገመንግሥታዊ መብት በማድረግ ያጸደቀችውን ዜና አድምጠን ሳናበቃ፣ ሰሞኑን ደግሞ ታላቋ ሀገር አሜሪካ ግብረሰዶማዊነት በመላ ሀገሪቱ ውስጥ ሕገመንግሥታዊ እንዲሆን አጽድቃለች፡፡ ይህን ተከትሎ ከመላው ዓለም ዘንድ የድጋፍና ተቃውሞ አስተያየቶች እየተሰጡ ነው፡፡
ወገኖች ሆይ፣ ዓለማችን በትልቅ ትኩሳት ቀልጣ ልትጠፋ ደርሳለችና በዚህ ልንደነቅ አይገባም፡፡ ግብረሰዶማዊነት በሀገር ደረጃ ሕጋዊ ከሆነባቸው ሀገሮች አሁን አሜሪካ 15ኛዋ ሀገር ትሁን እንጂ፣ ሌሎችም በርካታ ሀገሮች ሕጉን በመወሰኛ ምክር ቤቱ ጠረጴዛ ላይ ወረፋ አስይዘው ቀን እየጠበቁ ያሉ በርካታ ናቸው፡፡ በሀገራችንም ኢትዮጵያ በመወሰኛ ምክር ቤቱ ጠረጴዛ ላይ ይኼ ጥያቄ ወረፋ ይዞ ይኑር አይኑር የማውቀው ነገር ባይኖርም፣ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የግብረሰዶማዊያን ክለቦች የመኖራቸው እውነታ ከሐሜት ባለፈ ደረጃ ሲወራለት ቆይቷል፡፡
ይኼ ችግር በዓለም ደረጃ እያሳየ ከመጣው ፈጣን የሆነ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም አጋንንታዊ ጫና ሲታይ፣ በቅርብ ዓመታት በመላው የዓለም ሀገሮች ተቀባይነት የሚያገኝ ይመስላል፡፡ ስለሆነም፣ የዓመታት ጉዳይ ይሁን እንጂ ኢትዮጵያም ግብረሰዶማዊነትን በውዷ ሳይሆን በግዷ ተቀብላ በሕገመንግሥት የምታጸድቅበት ዘመን ሩቅ አይመስልም፡፡
ወገኖች ሆይ፣ ግብረሰዶማዊነት በመጽሐፍ ቅዱሳዊ እይታ ምንድነው? ግብረሰዶማነት ማለት ‹‹የማይገባውን ነገር እንዲያደርግ ተላልፎ የተሰጠ የማይረባ አእምሮ›› ማለት ነው፡፡ ይህ አእምሮ የሚፈጠረው እግዚአብሔር ለሰዎች ሊታወቅ እየፈለገና እየቀረበ ነገር ሰዎች እርሱን ለማወቅ ባለመውደድና ባለመፈለግ የሚከሰት አደጋ ነው፡፡ ይህን ሐሳብ በምሣሌ ላስረዳ፡፡
አንድ በሽተኛ ከታመመ ታክሞ መዳን ይገባዋል፡፡ ይህን ሕክምና ባልፈለገና ባልወደደ መጠን በሽታው ወደ ካንሰር ይቀየራል፡፡ ግብረሰዶማዊነት ከበሽታ ያለፈ የሰውን ስነልቦና ወደ እንስሳነት የሚቀይር ካንሰር ነው፡፡ የሰው ዓይነምድር መብላትን ጨምሮ ግብረሰዶማዊያን ሲያደርጓቸው የሚታዩት እጅግ ቀፋፊና ዘግናኝ የሆኑ ድርጊቶች ይህን እውነታ የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ግብረሰዶማዊያን የተቃራኒ ጾታ ግንኙነት የሚጠሉ ቢሆንም፣ ነገር ግን በሚገርም ሁኔታ እናት ከወንድ ልጅዋ ጋር፣ አባት ከሴት ልጁ ጋር፣ ወንድም ከእህቱ ጋር የሚያደርገውን የግብረሥጋ ግንኙነት ያበረታታሉ፡፡ ሴቶቹ ከወንድ ውሾች ጋር፣ ከወንድ ፈረሶችና ከወንድ አህዮች ጋር የሚያደርጉትን የግብረሥጋ ግንኙነት ያበረታታሉ፡፡ ወንዶቹም ከሴት ውሾች ጋር፣ ከሴት ፈረሶችና አህዮች ጋር የሚያደርጉትን የግብረሥጋ ግንኙነት ያበረታታሉ፡፡ ይህም ከተፈጥሮ ሕግጋትና ሥርዓት ጋር ያላቸውን ጥላቻ ያሳያል፡፡
ወገኖች ሆይ፣ ግብረሰዶማዊያን፣ የተቃራኒ ጾታ ግንኙነት የሚጠሉ ቢሆንም፣ አንዲት ሴት በአንድ ጊዜ ከሶስትና አራት ወንዶች ጋር የምታደርገውን የግብረሥጋ ግንኙነት ያበረታታሉ፡፡ ግብረሰዶማዊያን፣ የተቃራኒ ጾታ ግንኙነት የሚጠሉ ቢሆንም፣ ነገር ግን በሕዝብ አደባባዮችና በየመንገዱ ወንዶች ከሴቶች ጋር የሚያደርጉትን ከባሕልና ሥርዓት ያፈነገጠ ዝሙት እንዲደረግ ያበረታታሉ፡፡ ይህም ከተፈጥሮ ሕግጋትና ሥርዓት ጋር ያላቸውን ጥላቻ ያሳያል፡፡
ወገኖች ሆይ፣ ግብረሰዶማዊያን፣ የተቃራኒ ጾታ ግንኙነት የሚጠሉ ቢሆንም፣ ነገር ግን ሁለት ወንዶች ሚስቶቻቸውን ተቀያይረው፣ አንድ ቤትና አንድ አልጋ ላይ መዘሞትን ያበረታታሉ፡፡ ግብረሰዶማዊያን፣ የተቃራኒ ጾታ ግንኙነት የሚጠሉ ቢሆንም፣ ነገር ግን ወንዶች ሚስቶቻቸውን አስይዘው ወይንም አከራይተው ቁማር እንዲጫወቱባቸው ያበረታታሉ፡፡ ግብረሰዶማዊያን፣ የተቃራኒ ጾታ ግንኙነት የሚጠሉ ቢሆንም፣ ነገር ግን ወንዶች ሴት ሕጻናትን አስገድደው እንዲደፍሩ ያበረታታሉ፡፡ ይህም ከተፈጥሮ ሕግጋትና ሥርዓት ጋር ያላቸውን ጥላቻ ያሳያል፡፡
ወገኖች ሆይ፣ እነዚህ ነገሮች በኢትዮጵያ ውስጥም በኅቡዕ እየሆኑ ናቸው፡፡ አስቡት እስቲ 
በምዕራቡ ዓለም ሴቶች ወንድ ውሾችን ለመግዛት የሚመርጡበትና ከሰው በላይ ከአቅም በላይ ሲንከባከቧቸውና ሲወዷቸው የምናይበት ምክንያት፣ ወንዶች ሴት ውሾችን ለመግዛት የሚመርጡበት ምክንያትና ሩቅ መንገድ ሲሄዱም ይዘዋቸው ለመሄድ የሙጥኝ የሚሉበት ምክንያት የጤና ነው?
ወገኖች ሆይ፣ እስኪ በዚህ ዲቮሽን ላይ የሚሰማችሁን አስተያየት ስጡበት? ከሰማችሁትና ካነበባችሁት አካፍሉ? ስለግብረሰዶማነት ያለዎትን አቋም ያንጸባርቁ?

አለጊዜውም ጽና!!!!

ዲቮሽን 292/07 ሰኞ፥ ሰኔ 22/07
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
አለጊዜውም ጽና!!!!
እግዚአብሔርን ለምንፈራ ለእኛ፣ ሕይወት ሁልጊዜ አመቺ አይደለችምና፣ ያገኘነውን ያህል ስናጣ፣ ሰማይ ሲከደንብንና፣ መሔጃ መላወሻ ስናጣ፣ ቅድስናችንን ለመጣል፣ ብኩርናችንን ለማቃለል፣ ለጌታ ያለንን ነገር ለማዳፈንና፣ አማራጭ ያልነውን ነገር ለመያዝ እናስባለን። አንዳንዴም፣ በጽድቅና በሐጢያት መካከል ያለው ድንበር፣ ውሉ፣ ይጠፋብንና፣ ስሜታችንን ብቻ ወደ መታዘዝ እናደላለን። እግዚአብሔርን ከመፍራት የሚገኘው በረከትና ጥቅም ሁሉ ትርጉም የሚያጣብን ወቅት
ይኖራል።
የሚወዱን ከእኛ በራቁ ጊዜ፣ ብቸኝነት ሲሰማን፣ በቤተክርስትያንም፣ በሰፈርም፣ የምናየው ነገር አላምር ሲለን፣ ሲርበንና ሲጠማን፣ ስንራቆት፣ . . . ሕይወት ዳገት ሲሆንብን፣ ጸንቶ መገኘት እጅግ ፈታኝ ነገር ነው። ቢሆንም ግን፣ ከነገሮች ሁሉ በላይ የሆነውን፣ ኤልሻዳዩን እያሰብን፣ ጸንተን ልንኖር ይገባል። ለዚህም ነው፣ ጳውሎስ፣ አለጊዜውም ጽና በማለት፣ 2ኛ ጢሞ 4፡2 ጢሞቴዎስን የሚመክረው።
መንፈስ ቅዱስ ሆይ፣ ሁሉን ታደርግ ዘንድ በእርግጥ ቻይ ነህና፣ በዚህች ተለዋዋጭ ዓለም ውስጥ፣ ጸንተን እንድኖር እርዳን። ዓለምም በውስጧም ያሉ ገሮች ሁሉ አላፊና ቀሪ መሆናቸውን፣ ትሁት መንፈስ ቅዱስ ሆይ፣ አሁንም፣ አሁንም፣ ደግመህ ደጋግመህ፣ ሳትሰለችና ሳትታክት፣ እባክህ ለነፍሳችን
አስተምራት። እኛም መስማት እንዲሆንልን፣ መንፈሳዊ ዓይኖቻችንን አሁን አብራ። ሰምተህኛልና ተባረክ።
ትምሕርቱ ጠቅሞዎታል፣ እንግዲያውስ እባክዎ ላይክ፣ ሼር እና ኮሜንት ያድርጉ፣ ጌታ ይባርክዎ።

እንባህን እናፍቃለሁ

ዲቮሽን 291/07 እሁድ፥ ሰኔ 21/07
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
እንባህን እናፍቃለሁ
እንባህን እያሰብሁ በደስታ እሞላ ዘንድ . . . ። 2ኛ ጢሞ 1፡4
አማኝ መሆን ማለት፣ ውጫዊ መረጋጋት፣ ሰላም ሳይሆን ሰላም ነው ማለት፣ በጌታ መንፈስ ሳይነኩ፣ እንደተነኩ መምሰል፣ መንፈሳዊ ጨዋነት፣ መንፈሳዊ ሰላምታ፣ መንፈሳዊ አንደበት፣ መንፈሳዊ አለባበስ፣ የማስመሰል ቁጥብነት፣ . . . . . . ብቻ ከልብ ያልሆነ፣ ለታይታ ብቻ የምናደርገው ተግባር አይደለም።
አማኝነት፣ እግዚአብሔርን በየእለቱ የማወቅና የመረዳት ሒደት ነው። አማኝ፣ ይወድቃል፣ ይነሳል፣ ያለቅሳል፣ ይስቃል፣ ይጠይቃል፣ ይከፋዋል፣ አምላኬ ወዴት ነህ? ይላል። በግል ጉዳዩም ሆነ፣ በሀገርና በቤተክርስትያን ጉዳዮችም ላይ፣ ያልገባው ነገር ካለ፣ አማኝ ያለቅሳል፤ ይጨንቀዋል፤ ይጠበዋል።
ለዚህም ነው፣ ጳውሎስ፣ “እንባህን እያሰብሁ በደስታ እሞላ ዘንድ ላይህ እናፍቃለሁ፣ በአንተ ያለውን ግብዝነት የሌለበትን እምነትህን አስባለሁ” በማለት ለጢሞቴዎስ የሚጽፍለት።
አባት ሆይ ከማስመሰል ህይወት አውጣንና፣ የቀደመውን እንባችንን እና ቅንነታችንን መልስልን። ግብዝነት እና አስመሳይነት የተሞላው ሕይወታችን ዛሬ ይለወጥ። ሰምተህኛልና ተባረክ።
ትምሕርቱ ጠቅሞዎታል፣ እንግዲያውስ እባክዎ ላይክ፣ ሼር እና ኮሜንት ያድርጉ፣ ጌታ ይባርክዎ።

እውነተኛ አምልኮ

ዲቮሽን 290/07 ቅዳሜ፥ ሰኔ 20/07
(በዶ/ር በቀለ ብርሃኑ)
እውነተኛ አምልኮ
እውነተኛ አምልኮ በእግዚአብሔር ጸጋ ከተለወጠ ልብ ይወጣል፡፡ እውነተኛ አምልኮ ግብዝነት የሌለበትና እግዚአብሔርን በእውነትና በመንፈስ በማወቅ የተመሠረተ ስግደት ነው፡፡ እውነተኛ አምልኮ ራስን መስጠት ነው(ሮሜ 12፡1)፡፡ እውነተኛ አምልኮ መድረክ ላይ ከምናደርጋቸው ስርዓቶች ያልፋል፡፡ እግዚአብሔርንም በሚገባ ማወቅ መሠረቱ ነው፡፡
እውነተኛ አምልኮ በኑሮ፣ በዕለት ዕለት በምንሠራው ሥራና ከሰዎች ጋር በምናደርገው ግንኙነት ወዘተ ይገለጻል፤ የእግዚአብሔር ቃል አንዲህ ይላልና፡- “ነጻ የሚያወጣውን ፍጹሙን ሕግ ተመልክቶ የሚጸናበት፣ ሥራንም የሚሠራ እንጂ ሰምቶ የሚረሳ ያልሆነው፣ በሥራው የተባረከ ይሆናል። አንደበቱን ሳይገታ ልቡን እያሳተ እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር የእርሱ አምልኮ ከንቱ ነው። ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፤ ወላጆች የሌላቸውን ልጆች ባልቴቶችንም በመከራቸው መጠየቅ፣ በዓለምም ከሚገኝ እድፍ ሰውነቱን መጠበቅ ነው።” (ያዕቆብ 1፡25-25)
እውነተኛ አምልኮ በተግባር የተገለጠ ሕይወትንና ቅድስናን ይፈልጋል ማለቱ ነው፡፡ እነዚህ ሁለቱ ሳይሟሉ የሚደረጉ አምልኮ ተብዬዎች ግርግር ነው የሚሆኑት ማለቱ ነው፡፡ በእርግጥ ወደ ጎን አድናቆት ያተርፉ እንደ ሆነ ነው እንጂ፣ ወደ ላይ አያርጉም፡፡ ወደ ጎን ቲፎዞ ያስገኙ እንደ ሆነ ነው
እንጂ፣ በእሱ ዘንድ ተቀባይ አይኖራቸውም፡፡ የልብ አምላክ ስለሆነ፣ በምድራችን ቋንቋ ፍተሻውን(censorship) አያልፉም::
እውነተኛ አምልኮ ሐቀኝነትን፣ ጥልቅ ንስሐን፣ የተሰበረ መንፈስንና መታዘዝን ይፈልጋል፡፡ ነገር ግን በብዙዎቻችን ዘንድ ብዙ ነገሮች ነካ ነካ(superficial) እየሆኑ መጥተዋል፡፡ በኢሳይያስ ዘመን የነበሩ ሰዎች ከእኛ ዘመን ሰዎች ጋር እጅግ ይመሳሰላሉ፡፡ የጌታ መንፈስ አፋቸውና ልባቸው አልተገናኝቶ ስለሆነበት እንዲህ ብሏቸዋልና፡-
“ይህ ሕዝብ በአፉ ወደ እኔ ይቀርባል(ጸሎትና አምልኮ እንደ ልብ ነው)፣ በከንፈሮቹ ያከብረኛልና ልቡ ግን ከእኔ የራቀ ነው”(ኢሳይያስ 29፡13፣ አጽንኦት በእኔ የተጨመረ)
ይህ ሁኔታ በዚህ ዘመን የባሰ አይመስላችሁም? በግሌ እንደዛ አስባለሁ፡: ስለዚህ የሚበጀን ላይ ትንሽ ልበል፡፡ በእውነተኛ መመለስና በተሰበረ ልብ እሱ የሚፈልገውን አምልኮ ለመሰዋት እንችል ዘንድ፣ “ከኔ ምንድነው የምትፈልገው?” እንበለው፡፡ በእርግጥ በፊቱ ከምር ከወደቅን ለእያንዳንዳችን ምን ማድረግ እንደሚገባንና የቱ ጋ መስተካከል እንደሚገባን ያሳየናል፡፡ ያኔ ማለትም ውስጣችን በጸጋው ኃይል ከተሠራ በኋላ፣ ድንቅ አምልኮ ከመንፈሳችን ወደ ላይ ይወጣና ያርጋል፡፡ አዎ፣ ንጉሥ ሰለሞን የሠራው ቤተ መቅደስ ተሠርቶ ከተጠናቀቀ በኋላ፣ የእግዚአብሔር ክብር መቅደሱን እንደሞላው፣ ከተሠራ ማንነት የሚወጣ አምልኮ ልዩ ነው የሚሆነው፡፡
“አቤቱ፥ በውዴታህ ጽዮንን አሰማምራት፤ የኢየሩሳሌምንም ቅጽሮች ሥራ። የጽድቁን መሥዋዕት መባውንም የሚቃጠለውንም መሥዋዕት በወደድህ ጊዜ፣ያን ጊዜ በመሠዊያህ ላይ ፍሪዳዎችን ይሠዋሉ።” (መዝሙር 51፡
18-19)

ለጠላት - ፊት አይስጡ!

ዲቮሽን 289/07 አርብ፥ ሰኔ 19/07
(በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)
ለጠላት - ፊት አይስጡ!
የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፥ ንጉሥ ሆይ! ነገር ግን፥ ንጉሥ ሆይ፥ እርሱ ባያድነን፥ አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ አሉት (ዳንኤል 3 : 17-18)
ወዳጄ ሆይ፥ የሚያመልኩትን ጌታ ማንነቱን ያውቃሉ? ግርማና ሞገሱን፥ ኃይልና ሥልጣኑን፥ ችሎታ ብቃቱን ጉልበትና ክንዱን ያውቃሉ? እንግዲያውስ ለጠላትዎ ዛቻ፥ ስድብ ማስፈራሪያ አይንቀጠቀጡ! አምላክዎን ካወቁ፥ ለጠላት ፊት አይስጡ!
በባቢሎን አውራጃ በፖለቲካ ሥልጣን ላይ ተሿሚዎች የነበሩ ሲድራቅ ሚሳቅና ሲብደናጎ አምላካቸውን የሚያውቁ፥ አይሁዳዊያን ናቸው፡፡ የመንግሥታቸውን አዋጅ፥ አዋጅ መተላለፍ የሚያመጣውን ቅጣት ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ የንጉሡ ቁጣ፥ የባለሥልጣናቱ አድማ በሕይወታቸው ላይ የሚያስከፍላቸውን ዋጋ ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ ነገር ግን፥ ይህን ሁሉ እያወቁ፥ በነፍሳቸው ተወራርደው ለሐውልቱ ላይሰግዱ፥ ለባለሥልጣናቱ ለንጉሡም ላያጎበድዱ ውሳኔ አደረጉ!
ወገኖች ሆይ፥ ሲድራቅ ሚሳቅ አብደናጎ፥ ለንጉሡ ሐውልት ሰግደው በሕይወትና በምድራዊ ክብር ከመኖር ይልቅ፥ በሚነድደው እሳት መጣልን መረጡ፡፡ ለጣዖት በመስገድ ምድራዊ ሀብትና ሥልጣን ከሚያቆዩ፥ ለሚያመልኩት ጌታ መሰዋት መረጡ!
ወዳጄ ሆይ፥ የሚያመልኩትን ጌታ በእውነት ያውቁታል? ክብርና ሞገሱን፥ ኃይልና ሥልጣኑ ችሎታ ጉልበቱንስ ያውቃሉ? እንግዲያውስ ለጠላት ማስፈራሪያ ወድቀው አይስገዱ! ፈተና ቢነሳ፥ ማዕበል ቢበረታ ለወጀብ ለንውጥውጥታ ፊትዎትን አይስጡ!
ወገኖች ሆይ፥ ዳዊትን ያስቡ! በጎልያድ ፊት ሲቆም ለዛቻ ፉከራው አልተንቀጠቀጠም! ዳንኤልን ያስቡ! በአንበሶች ጉድጓድ ሲጣል የሚያመልከውን ያውቅ ነበርና አልተብረከረከም! ዮሴፍ ለጶጥፋር ሚስት አልተልፈሰፈሰም! ነህምያም ለሰንበላጥ ለጦቢያና ጌሳም የዛቻ፥ የንቀት፥ የመግደል ሙከራ አልተርበደበደም!
ወገኖች ሆይ፥ የሚያመልኩትን አምላክ ያውቃሉ? እንግዲያውስ፥ ለጠላት ፊት አይስጡ!

የማይሰማ ጩኸት !

ዲቮሽን 288/07 ሓሙስ ስኔ 18/07
( ጌታሁን ሓለፎም )
የማይሰማ ጩኸት !
“ጌታ ሆይ ማን ምስክርነታችንን አመነ? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገለጠ ?” (ዮሓ 12፡-38)
ወጭ አውጥቶ፥ ለፍቶበት እና ብዙ ተጨንቆ አስቦ አልሞ ሽር ጉድ ብሎ ያዘጋጀውን ግብዣ ታዳሚው በሰአቱ መጥቶ ሲበላ ሲጠጣ ሲያይ ጋባዥ ደስ ይለዋል ፡፡ ከደስታውም ብዛት “ብሉልኝ ጠጡልኝ ” እያለ አደግድጎ ያስተናግዳል፥ በተለይ እማ የምግቡ ጣእም እና መስተንግዶውን መልካም እንደነበረ እያደንቁ “ አቤት አቤት እንዲህ ነው እንጅ ግብዣ ማለት እጅ ይባረክ ብለናል” እያሉ ስለ ግብዣው ሲያመሰግኑ ሲመርቁ
ጋባዥ ጆሮ ውስጥ የገባ እንደሆነማ ፤ ይኮራል ፤ ሓሴት ያደርጋል ደስታው ወሰን ያጣል ፡፡ ልፋቱ ከንቱ እንዳልቀረ ያስባል ፡፡
ሰው የወለደውን ሲስሙለት ፤ ልጆቹ አድገው ለቁም ነገር ሲበቁለት ፤ ስራውን ሲያደንቁለት ፤ በርታ አይዞህ ሲሉት ይወዳል፡፡ ምክሩ ሲደመጥለት ፤በሸንጎ ለመፍትሄ ሲፈለግ ኩራት ይስማዋል
በአንጻሩ ግን ገንዘቡን አቅሙን አሟጦ ጉልበቱን ያፈሰሰበት ግብዣ ላይ ፤ ታዳሚው ሳይመጣ ቢቀር የተዘጋጀው ድግስ በይ ቢያጣ ፤ ሰው የመከረው ምክር በሰዎች ዘንድ ዋጋ ቢስ ቢሆን ፤ ባይደመጥ ፤ የመፍትሔ ሃሳብ እንዳለው ውስጡ እያወቀ ምክሩን ቢያጣጥሉበት ያ ሰው ይከፋል ያዝናል ፡፡
አዎ እንዲሁ ነው ነብዩ ኢሳያስም ስለ ክርስቶስ እየሱስ ያለውን መረዳት ስለ አምላክነቱ ስለ ጌትነቱ ስለሁሉን ቻይነቱ ስለአዳኝ እና ታዳጊነቱ የገባውን እውነት ቢሰብክ ቢመሰክር ሰዎች ስለአልተረዱት አዘነ ውስጡ ተሰበረ ፡፡ አሻግሮ የመሲሁን መምጣት ቢያይ ፤ በውስጡ የበራለትን ብርሃን ለሰዎች ሊያስረዳ ቢፈልግ ሰሚ ቢያጣ እንዲህ አለ “ ጌታ
ሆይ ማን ምስክርነታችንን አመነ የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገለጠ ?”
“ ጌታ ሆይ ለኛ የተገለጠልንን እውነት የዳንበትን ተስፋ በውስጣችን ያፈሰስከውን የማያሳፍር ፍቅር ለሰዎች ብንናገር ብንመሰክር አላመኑንም ምድር እና ሰማይን የፈጠርክበት ጥበብህ ለማን ተገለጠ ማን ተረዳው እኛም ብንናገር ሊሰሙን ፈቃደኞች አይደሉም ” አለ ፡፡
ዛሬም ቢሆን እንዲሁ ነው የነበያት ጩኸት ሰሚ አጥቷል ፤ የውንጌላዊያን ድምጽ አልተደመጠም የሰባኪዎች ምስክርነታቸው ጆሮ አላገኘም ስለ ጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት የሚነገረው የዛሬ 2000 አመት በፊት ጀምሮ የሚሰበከው ወንጌል በውስጡ ህይወት እያለበት ሰወችን ከሞት የሚታደግ ስልጣን ቢኖረውም ዛሬም ድረስ እየተገፋ ይኖራል
በምትኩ የሰው ልጅ ፡ እግዚአብሔር ለተጸየፈው እና ሓጢያት ነው ብሎ ለጠላው ለዘፈን እና ለዳንኪራ ለተለያየ ክፋት እንድሁም ለርክሰት ሲጋፋ እና አዳራሹን ሲሞላ ሲያጣብብ ፤ በየስፍራው የሰዎች ልጆች በጥፋት ወጥመድ ለመያዝ ሲቸኩሉ ህይወት መንገድ እና እውነት የሆነውን ክርስቶስ እየሱስን ሲገፉ ስለ መሲሁ ሲነገር ሳያደምጡ እና ጆሮ
ሳይሰጡ ዛረም ድረስ አሉ ፡፡
ምናለ ጌታ ሆይ ሰው ሁሉ አንተን አምኖ የዘላለምን ህይወት ቢወርስ ?
ምናለ ጌታ ሆይ በተለያየ እስራት ውስጥ ያለ ወደ አንተ መጥቶ ነጻነትን ፤ መፈታትን ቢያገኝ ?
ምናለ ጌታ ሆይ እንዲያው ይሔ ቃል ለሁሉ ሰው ቢበራለት ? “መዳን በሌላ በማንም የለም ልንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና ” ሓዋ 4፡-12
ምናለ ጌታ ሆይ ይህ የርህራሄ ቃልህ ለሁሉ ቢገለጥ ? “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ህይወት እንዲኖረው እንጅ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ አለሙን እንዲሁ ወዷል እና ” ዮሓ 3፡-16

Wednesday, June 24, 2015

የሚጓጉለትን ሳያዩ - አይሙቱ!

ዲቮሽን 287/07 ረቡዕ ሰኔ 17/07
(በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)

የሚጓጉለትን ሳያዩ - አይሙቱ!

(ስምዖን) በጌታም የተቀባውን ሳያይ ሞትን እንዳያይ በመንፈስ ቅዱስ ተረድቶ ነበር (ሉቃስ 2 : 26)
ወገኖች ሆይ፥ በሕይወታችን ሳናይ ላለመሞት የምንጓጓለት ነገር ምንድነው? በውስጥ ሰውነታችን የተረዳነው፥ በመንፈስ ቅዱስም ያረጋገጥነው፥ በትንቢት የተነገረን፥ ከቃሉ የሰማነው ነገር ምንድነው?

ወዳጄ ሆይ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያረጋገጥልዎትን፥ በሕይወት ዘመንዎ በዓይን በብረትዎ እንደሚመለከቱ፥ መውጣትና መውረስ መውሰድ እንደሚችሉ የተናገረዎትን ሳያዩ ሳይመለከቱ፥ ሳይወስዱና ሳይወርሱ መሞት የሚባል ነገር አይመለከቱም! የተነገረዎትን ከመጠበቅ ይልቅ፥ በገዛ ፈቃድዎ ካላበላሹ በቀር፥ ከጥበቃው ማማ ካልወረዱ በቀር፥ ከሕይወት ሩጫው መስመር አቋርጦ ለመውጣት ካልወሰኑ በቀር፥ የተገባልዎትን ቃል ሳይመለከቱ ደግሞም ሳይወርሱ ሊሞቱ አይችሉም!

ወዳጄ ሆይ፥ ከስምዖን ይማሩ! ጻድቁ ስምዖን በጌታ የተቀባውን ሳያይ ሞትን ላለማየት አሻፈረኝ አለ፡፡ የተቀባውን ሳያይ የሞትን እንግዳ አልቀበል አለ፡፡ የተቀባውን ሳያይ ሞት በሩን ሲያንኳኳ እንዳልሰማ ሰምቶ አልከፍትለት አለ፡፡ እስኪያረጅ እስኪገረጅፍም ድረስ የሞትን ጥሪ "አልሰማም-አላይም-አልቀበልም!" አለ፡፡ በመጨረሻም የተመኘውን ጌታ በዓይኑ በብረቱ ሊመለከት ቻለ፡፡ የተቀባውን አቅፎ ሊስመውም ቻለ! ሃሌሉያ!

ወዳጄ ሆይ፥ የኔም ጸሎት ይኼ ነው! የተነገረኝን ተስፋ፥ የተገባልኝን ቃል፥ ሳላይ ሳላገኘው ሳልወርሰው አልሞትም! ሞት በመንገዴ በድንገት አግኝቶኝ እኔን ሊጨብጠኝ እጁን ቢዘረጋ፥ ጠልፎ እንዲጥለኝ ካልታሰበ ቦታ ወጥመድ ቢዘረጋ፥ ቃል ያለኝ ሰው ነኝና ሞትና መልዐኩ ሊያገኘኝ አይችልም! የምጓጓለትን ሳልወርሰው አልሞትም!

ወዳጄ ሆይ፥ ላረጋግጥልዎት፥ የሚጓጉለትን ሳይወርሱ እርስዎም አይሞቱም! እንደ ጻድቁ ስምዖን፥ የተስፋ ቃልዎትን ሙላት፥ የሕዝብዎትን መጽናናት ከተጠባበቁ፥ በጽድቅና ትጋት መቆየት ከበቁ፥ በመንፈስ ቅዱስ ላይ መደገፍ ከቻሉ፥ የሚጓጉለትን ሳይወርሱ አይሞቱም!

Tuesday, June 23, 2015

በሕንጻ ግንባታ ለተጠመዱ አብያተክርስቲያናት!

ዲቮሽን 286/07 ማክሰኞ ሰኔ 16/07
(በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)

በሕንጻ ግንባታ ለተጠመዱ አብያተክርስቲያናት!

የእግዚአብሔርንም ሕግ መጽሐፍ አነበቡ፤ ዕዝራም እግዚአብሔርን ማወቅ ያስተምርና ያስታውቅ ነበር፥ ሕዝቡም የሚነበበውን ያስተውሉ ነበር። ( ነህምያ 8 : 8)

የነህምያ መጽሐፍ በምናነብበት ጊዜ ከምርኮ ተመላሽና ሳይማረኩ የቀሩ እስራኤላውያን የቃልኪዳን ምድራቸውና የገዛ ርስታቸው በሆነች ግዛታቸው ላይ አጋጥሟቸው የነበረውን የስነልቦና፥ የመንፈስና የሞራል ውድቀት፥ እንዲሁም ማኅበራዊ፥ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክስረት ለመለወጥ ያደረጉትን የሕዳሴና መልሶ ግንባታ ተጋድሎ ያሳያል፡፡

በነህምያ አመራር የፈራረሰችውን የእስራኤልን ቅጥር መልሶ የመገንባቱ ራዕይ በተሳካ ሁኔታ ፈር እንደያዘ፥ ወዲያው ደግሞ እዝራ የሕዝቡ መንፈሳዊ ሕይወት መልሶ ግንባታ ቦታ እንዲይዝ ሲሰራ እንመለከታለን፡፡

እዝራ በሕንጻ ግንባታ ለተጠመዱ እስራኤላዊያን የእግዚአብሔርን ሕግ መጽሐፍ እያነበበ፤ እግዚአብሔርን ማወቅ ያስተምርና ያስታውቅ ነበር፡፡ ሕዝቡም ደግሞ እዝራ የሚያነብበውን ቃል ያስተውሉ ነበር። ይህም በመሆኑ፥ በምድሪቱ ላይ ከጫፍ ጫፍ የሚደርስ ሪቫይቫል ተቀጣጠለ፡፡

ወገኖች ሆይ፥ በሀገሪቱ ሪቫይቫል ሲመጣ፥ ቀደም ሲል ወድቆ የነበረው የሕዝቡ ስነልቦና፥ የመንፈስና የሞራል ውድቀት፥ እንዲሁም ማኅበራዊ፥ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክስረት በመለኮታዊ ኃይል ተቀየረ! በመላ ሀገሪቱ ከዳር እስከዳር የምስጋናና የድል ዜማ ይደመጥ ጀመረ!

ወገኖች ሆይ፥ በሀገራችን በኢትዮጵያ ካለፉት አስርት ዓመታት ወዲህ መላው የኢትዮጵያ አብያተክርስቲያናት ከከተማ እስከ ገጠር በሕንጻ ግንባታ ስራዎች ላይ ተጠምደው፥ በተቃራኒው ደግሞ የሕዝቡ መንፈሳዊ ግንባታ ተስተጓጉሎ ወይንም ችላ ተብሎ እናያለን፡፡ ለሕንጻ ስራ ፕሮጀክቶች ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ፥ መንፈሳዊ ግንባታው ግን ተዘንግቶ እንታዘባለን፡፡

በሕንጻ ግንባታ ፕሮጀክቶች ላይ በከፍተኛ ደረጃ ተጠምደው የሚገኙ የኢትዮጵያ አብያተክርስቲያናትና የሕዝቡን መንፈሳዊ ግንባታ ቸል ያሉ መሪዎች፥ ከእዝራና ከነሀምያ ይማሩ!

መሪዎች ሆይ፥ ከሕንጻ ግንባታችሁ ጎን ለጎን፥ ለሕዝቡ የእግዚአብሔርን ቃል የማስተማሩን ስራ አትዘንጉ፥ ለቁሳቁስ በምትሰጡት ትኩረት መጠን፥ ወይንም ከሕንጻ ፕሮጀክቶች ይልቅ ለእግዚአብሔር ሕዝብ መንፈሳዊ ዕድገት ትልቅ ትኩረት ስጡ፡፡

መሪዎች ሆይ፥ መንፈሳዊ ፕሮጀክቶችን ችላ አትበሉ! ሕዝቡ እግዚአብሔርንና ቅዱስ ቃሉን እንዲያውቅ ትጋትን ጨምሩ፡፡ ከእዝራ ከነህምያ፥ ይህንን ተማሩ!

Sunday, June 21, 2015

ምርኮን ተካፈለች

ዲቮሽን 285/07 ሰኞ፣ ሰኔ 15/07
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
ምርኮን ተካፈለች
በቤትም የምትኖር ምርኮን ተካፈለች። መዝ 68፡ 12
ከእግዚአብሔር ጋር በሚኖረን ሕብረት፡ አንዳንዴ መልካም የምንላቸው ጊዜያት፣ አንዳንዴም ከባድ የምንላቸው ወቅቶች ይኖራሉ። አንዳንዴ በበረከት ላይ በረከት እየተደራረበልን ለመቁጠር ያስቸግረናል፣ አንዳንዴም በፍጹም ማጣት እና መራቆት ውስጥ እናልፋለን። አንዳንዴ በምስጋናና በዝማሬ ስንጥለቀለቅ አንዳንዴም በልቅሶና በፍርሃት፣ እንሰጥማለን።
አንዳንዴ ደግሞ፣ በእምነት ስንሞላ አንዳንዴም ደግሞ በጥርጣሬና በስጋት እንዋጣለን። አንዳንዴ ደግሞ በሞገስ ስንወጣ፣ አንዳንዴ ደግሞ በውርደት አንገታችንን እንደፋለን።
ሞላም ጎደለ ግን ዋናው ነገሩ፣ ስንችል እየዘመርን፣ ሲያቅተን እያለቀስን፣ ሲሆንልን በብርታት፣ ሳይሆንልን በድካም፣ ሲደላን እየበረርን፣ ሳይደላን በእንብርክካችን ሆነን፣ በጌታ ቤት፣ በመንፈሱ አፀድ ውስጥ መገኘትን የመሰለ ትልቅ ቁምነገር የለም።
ምክንያቱም፣ አንድ ቀን፣ ጌታ ልጆቹን ሊያስብ በሚመጣበት ቀን፣ ምርኮ ተካፋዮች መሆናችን የማይቀር እውነት ነው። ጌታ በእርግጥ፣ ወደ እያንዳንዳችን ነገር መምጣቱ አይቀርም። ዛሬ ላይ፣ ይህ ነገር እውነት ባይመስለንም፣ በእርግጥ ጌታ መምጣቱ አይቀሬ ነው። ያኔ ግን፣ በቤቱ መገኘት ይሁንልን።
ጌታ ልጆቹን ሊጎበኝ ሲመጣ እንዳያጣን፣ በቤቱም የተገኙት ምርኮ ሲካፈሉ፣ እኛ በደጅ እንዳንቀር፣ የበረከት ዝናብ መውረዱንም በዝና ብቻ ሰሚዎች ሆነን፣ ተካፋዮች ሳንሆን ግን እንዳንቀር፣ በምንም ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ብንሆን፣ በቤቱ ውስጥ እንገኝ።
አባት ሆይ፣ ሁሉን ታደርግ ዘንድ ቻይ ነህና፣ ዛሬ፣ የተፍገመገምነውን ሁሉ፣ በክንፎችህ ጥላ ውስጥ ሸሽገን። ሰምተህኛልና አመሰግንሃለሁ።
ትምሕርቱ ጠቅሞዎታል? እንግዲያውስ፣ እባክዎ ላይክ፣ ሼር
እና ኮሜንት ያድርጉ፤ ጌታ ይባርክዎ።

ዲቮሽን ይቋረጥ ወይስ ይቀጥል? A) ይቋረጥ B) ይቀጥል

ማስታወቂያ፣

ዲቮሽን ይቋረጥ ወይስ ይቀጥል?
A) ጠቃሚ ስላልሆነ ይቋረጥ
B) ጠቃሚ ስለሆነ ይቀጥል

መረጥሁ!!!

ዲቮሽን 284/07 እሁድ፣ ሰኔ 14/07
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)

መረጥሁ!!!

በእግዚአብሔር ቤት እጣል ዘንድ መረጥሁ። መዝ 84፡ 10

መቼም በዚህ ምድር ላይ ያለ ነገር ሁሉ አላፊ ነው። ወይ እኛ እናልፋለን፣ ወይም ያ የጓጓንለት ነገር ያልፋል፣ በመጨረሻም ሰማይና እና ምድር እንኳን ያልፋሉ። ብቻ ምናለፋችሁ፣ በዚህ ምድር ላይ ቋሚ የሆነ አንዳችም ነገር የለም።

ስለዚህ፣ ዛሬ፣ ለዚህ ምድር ሆይ ሆይታ እና አጓጓል ድንዛዜ፣ ምኞት እና ግርግር ልዩ የሆነ “እምቢ ለእርኩሰት” የሚያሰኝ የጭካኔ መንፈስ እንዲገባብን እኔ እጸልያለሁ።

ዳዊት በኃጥአን ድንኳኖች ከመቀመጥ ይልቅ፣ በእግዚአብሔር ቤት እጣል ዘንድ መረጥሁ፣ ያለው እኮ፣ “ጸሎቴም ባይመለስ፣ የምፈልገውን ዝናና ክብርም ባለገኝ፣ በድህነት በበሽታም ብኖር፣ በማጣት በጉስቁልናም ብመታ፣ በውርደትና በነቀፌታ ብመላለስም፣ የምፈልገውን የአገልግሎት ደረጃና ስልጣን ባላገኝም፣ ያማረኝን ባልለብስና ባልጠጣም፣ አሪፍ መኪናና ቤት ባይኖረኝም፣ ሰዎች የሚገባኝን ከበሬታ ባይሰጡኝም፣ የያዝኩት ሁሉ ከእጄ ቢበተን፣ . . . ሌላ ቦታ ሄጄ፣ ይህን ሁሉ ከማገኝ፣ ከአምላኬ ጋር ተስማምቼ፣ ፈቃዱን ብቻ አድርጌ፣ ደስ የሚያሰኘውን ነገር ብቻ ሆኜለት፣ ህይወቴ ትለፍ” ማለቱ ነው እኮ።

ደግሞስ፣ እውነት እንነጋር ከተባለ ማነው እግዚአብሔርን ተደግፎ፣ አምኖና ተመርኩዞ ከበጎ ነገር ሁሉ የጎደለ! ዳዊት ይህን ሲል እኮ፣ እግዚአብሔርን በደንብ አድርጎ ስለሚያውቀው፣ አንዳችም ነገር እንደማያጣ አውቆም ጭምር ነው።
ወዳጅ መንፈስ ቅዱስ ሆይ፣ ዛሬ አእምሯችንን አይናችንን ልባችንን እጃችንን እግራችንን . . . ሁለንተናችንን ትቆጣጠር ዘንድ በኢየሱስ ስም ጸለይኩ። ሰምተህኛልና ተባረክ። አሜን።

ትምህርቱ ጠቅሞዎታል? እንግዲያውስ እባክዎ ላይክ እና ሼር ኮሜንትም ያድርጉ፤ ጌታ ይባርክዎ።

እየጨመረ የሚሄድ ሕይወት

ዲቮሽን 283/07፥ ቅዳሜ፥ ሰኔ 13/07
(በዶ/ር በቀለ ብርሃኑ)

እየጨመረ የሚሄድ ሕይወት

የጠለቀ መንፈሳዊ ጉዞ ለመጓዝና እየጨመረ የሚሄድ ርካታና እረፍት እንድናይ ካስፈለገ፣ የክርስትና ሕይወት ትጋትን ይጠይቀናል(ዕብ 4:11)፡፡ ትጋታችን በጨመረ ቁጥር፣ የእግዚአብሔር ጸጋ በሕይወታችን እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ለመንፈሳዊ ነገር ያለን መሻት እያደገ ይሄዳል፡፡

በእንደዚህ ዓይነት ግሥገሣ ውስጥ ባለማሰለስ ስንገኝ፣ እሱን ለማወቅ ያለን ራብ እየተለቀ ስለሚመጣ፣ እየጨመረ ለሚሄድ ፍለጋ እንጠናከራለን፡፡ ይህንን በእንግሊዝኛው አገላለጽ positive vicious cycle ይሉታል፡፡ ማለትም ትጋቱ የጨመረ መንፈሳዊ ራብን ይወልዳል፤ የጨመረ መንፈሳዊ ራብ ደግሞ ሌላ ከፍ ያለ ትጋትን ይወልዳል - መቸም ኡደቱ ማቆሚያ የለውም እኛ በሥጋዊ አካሄዶች እስካላጠፋነው ድረስ!

እየጨመረ የሚሄድ የክርስትና ሕይወት ብዙ ግብዓቶችን ይፈልጋል፡፡ መልካም የእምነት ውጊያንና ዲያቢሎስን በኃይል ጸንቶ መቃወም ይጠይቃል፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል ሳይታክቱ ማሰላሰልና በፊቱ ጥሩ የሆኑ ጊዜዎችን ማሳለፍ ግድ ይለናል፡፡ ሁኔታዎችንና ሥጋችንን ሳናዳምጥ የሚከፈሉ ዋጋዎችን እንደ ጌታ ፈቃድ መክፈልን ይጠይቀናል፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ ሕይወቴን የቀየረና ብዙ ቦታ ደጋግሜ የምጠቅሰውን መርሕ እዚህ ጋ ልጥቀስ፡፡ ሦስት በተሰናሰለ መንገድ የተቀመጡ ድርጊቶች በውጤት ሂደት እንዲህ ተቀምጠዋል፡-

ድርጊት(Action)------->ልማድ(Habit)------->ጠባይ(character)
ይህንን መርሕ ለመግለጽ ጸሎትን እንደ ምሳሌ ልውሰድ፡፡ ጸሎትን ደጋግመን ስናደርገው ወደ ልማድነት ይቀየራል፡፡ በሕይወታችን ልማድ እየሆነ ያለውን ይህንን ተግባር እየጨመርን ደጋግመን ስናደርገው ጠባያችን ወይም መገለጫ ባሕርያችን ይሆናል፡፡ ከዚያማ ውጤቱ እንዲህ ይሆናል፡- መጸለይ እንጂ አለመጸለይ አንችልም፡፡ በፊቱ መሆን እንጂ አለመሆን ያቅተናል - የሚጓጓለት ድንቅ ለውጥ!

የላይኛውን ሐሳብ የሚደግፉና የክርስትና ሕይወት እየተቀጣጠለ፣ እያደገና እየጨመረ የሚሄድ ሕይወት እንደ ሆነ የሚጠቁሙ ብዙ ክፍሎች አሉ፡፡ ለምሳሌ ሦስቱን ልጥቀስ፡-እስከ እግዚአብሔር ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ (ኤፌሶን 3፡19)፤ በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ (ሮሜ 12፡11)መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና/ብዙ የሚያሰክሩ ነገሮች እንዳሉ ልብ ይሏል/(ኤፌሶን 5፡16-20) የእግዚአብሔር ሰው ስሚዝ ዊግልስዎርዝ እንዲህ ብሎ ነበር፡- “በዛሬው ቀን ትላንትና የነበርክበት ቦታ ላይ ከተገኘህ የኋሊት እየሄድክ ነው"
በተሰጠ ማንነት፣ ልባችን መሉ በሙሉ በጌታ ላይ ሆኖ ከላይ በተጠቀሰው ዓይነት ፍለጋ(craving) እና ትጋት ስንቀጥል፣ የጌታ አብሮሆት ከመቸው በሚበልጥ ሁኔታ በሕይወታችን ዕውን ይሆናል፡፡ ከዚህም የተነሣ የምናገኘው የመጀመሪያው በረከት በቃላት ልንገልጸው የማንችለው ሰላም፣ መረጋጋትና ደስታ ይሆናል፡፡ መንፈሳዊ መረዳታችንም እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ጌታን በሚገባ እያወቅነው እንመጣለን፡፡ መንፈሳዊ ዓይኖቻችን በጨመረ ሁኔታ እየተከፈቱ ስለሚመጡ፣ ብዙ ረብ የሌላቸውን ነገሮች የመጣል መነሣሣትና አቅም እያገኘን እንመጣለን፡፡

እንደዚህ በጽናት ሳናሰልስ የጌታን ፊት በጨመረ ሁኔታ በፈለግን ቁጥር፣ የእግዚአብሔር ኃይል በውስጣችን እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ብዙ ቀንበሮች ከሕይወታችን ይሰበራሉ፡፡ ስለዚህም ከበፊቱ ይልቅ በሕልውናው ውስጥ መቆየት አያስቸግረንም፡፡ ብዙ ሰዓት በፊቱ መሆንም ያለ ጥርጥር ፈቃዳችን ይሆናል፡፡

ቃሉ ተግተው የሚሹኝ ምስጉኖች/የተባረኩ ናቸው(ምሳሌ 8፡34) ይላልና፣ ለሚሹት በታማኝነት የሚገለጠው ጌታ ሕይወታችን ሲጎበኝ የሚመጣው ለውጥ ለሌሎች በረከት ያደርገናልና በጨመረ ሁኔታ ተግተን እንፈልገው!
ጌታ ሆይ እርዳን!!

“አሁን እንዳገኘሁ ወይም አሁን ፍጹም እንደ ሆንሁ አይደለም፣ ነገር ግን ስለ እርሱ በክርስቶስ ኢየሱስ የተያዝሁበትን ያን ደግሞ እይዛለሁ ብዬ እፈጥናለሁ። ወንድሞች ሆይ፣ እኔ ገና እንዳልያዝሁት እቈጥራለሁ፤ ነገር ግን አንድ ነገር አደርጋለሁ፤ በኋላዬ ያለውን እየረሳሁ በፊቴ ያለውን ለመያዝ እዘረጋለሁ” ፊልጵስዩስ 3፡7-13)

ሕብረት እና ስኬት

ዲቮሽን 282/07፥ አርብ፥ ሰኔ 12/07
(በወንድም አበባዬ )

ሕብረት እና ስኬት

" አንዱም አንዱን ቢያሸንፍ ሁለቱ በፊቱ ይቆማሉ፤ በሦስትም የተገመደ ገመድ ፈጥኖ አይበጠስም። "(መጽሐፈ መክብብ 4:12)

ከ ኢየሱስ ጋር አዲስ ግንኙነት በጀመርኩባቸው የመጀመሪያ
ዓመታት የመንፈሳዊ ዕድገት ሶስት መሰረቶች ተብየ
ከተማርኳቸው ነገሮች ውስጥ አንዱ ሕብረት ነበር። ( ሌሎች
ሁለቱ ፀሎት እና የእግዚያብሄር ቃል ናቸው) ድስት በሦስት
ጉልቻ እንደሚቆም አማኝም ያለ እነዚህ ሦስቱ አይቆምም
ሲል መንፈሳዊ አባቴ ያሰተማረኝን አልረሳውም። በቃሉ እና
በፀሎት የበረታን ብንሆንም ከ ሌሎች አማኞች ጋር ጤናማ
ሕብረት ከሌለን ዕድገታች ምልዑ አይሆንም።
ይህ ጊዜ ከመቸውም ጊዜ በላይ ግለኝነት የተንፀባረቀበት
ጊዜ ነው። ግለኝነት እራሱ አንዱ የድህረ ዘመናዊነት
አስተሳሰብ ውጤት ነው። ሰዎች ከራሳቸው እና የራሳቸው
ከሆነው በላይ ለማንም የማይጨነቁ ይመስላል።
ለስኬታቸውም ሆነ ለውድቀታቸው የሌሎች ሚና እዚህ ግባ
የማይባል እንደሆነ የሚስቡ ይመስላል። ይህ ከመፅሐፍ
ቅዱሱ የሕይወት ፍልስምና ጋር ይጋጫል።

ሕብረት የክርስትና ሕይወት አንዱ ቁልፍ ነው። ለመንፈሳዊ
ሕይወታችንም ዕድገት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ግልፅ ነው።
ከምንም በላይ ግን ከስኬት እና ውጤታማነት ጋር ከፍተኛ
ቁርኝት አለው።

በሕይወታችን እና በአገልግሎታችን እንዲሳካልን ካስፈለገ
ጤናማ ሕብረት ሊኖረን ያስፈልጋል። እኛው በእኛው ለኛው
የሆነ ህይወት እና አግልግሎት የለም። በቤተክርስቲያንም
ሆነ በሌሎች ተቋማት በሚኖረን ተሳትፎ በሕብረት ልናምን
ይገባል። አንደኛው ዘርፍ ከሌላው ጋር በሕብረት ተቀናጅቶ
ካልሰራ ስኬት ላይ አይደረስም። በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ
የተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች ተናበው እና እርስ በርስ
ተደጋግፈው በሕብረት ሲሰሩ የሚያሰማ ውጤት ይመጣል።
አሁን አንዳንድ ቦታዎች ላይ እንደሚታየው አንዱ የአንዱን ስራ
በሚያንቋሽሽበት እና በሚያፈርስበት ሁኔታ ግን ለውጥ
ሊመጣ አይችልም። "አንድ ሰው አስቦ በአንድ በሬ ስቦ"
እንደሚባለው ማለት ነው።

ወገኖቼ እየተፈታተነን ያለውን ግለኝነት ልናሸንፈው ይገባል።
ለሕይወቴ እና ለስኬቴ ሌላው ወንድሜ ያስፈልገኛል
የሚለውን የቀደመ አስተሳሰብ ልናዳብር ይገባል። በግላችን
ምንም እንኳን ጥቂት ርቀት ልንሄድ የምንችል ቢሆንም የትም
ደረጃ ልንደርስ ግን እንደማንችል ልናምን ይገባል።
አሁን ቤተክርስቲያን ልዩነታቸውን አስፈተው በመቀናናት እና በ
መገፋፋት የሚነካከሱ ሳይሆን በ ጋራና በጤናማ ሕብረት
የሚሰሩ የተናበቡ አገልጋዮችንና ኣና አማኞችን ትፈጋለች።
የራሳቸውን ምኞት አረፋ እየደፈቁ በእኔነት መንፈስ ሕዝቡን
ግራ የሚያጋቡ መንጋውን የሚበትኑ ሳይሆን ቀርበው በፍቅር
የሚያቅፉትን ሰፊ ትክሻ ያላቸው እና በሕብረት የሚያምኑ
መሪዊችን ትፈልጋለች። አሁን አገራችን በራሳቸው የብልፅግና
ምኞት ሰክረው ሁሉን እንደ ማግኔት ወደራሳቸው የሚስቡ
ስግብግቦችን ሳይሆን በጋራ የሚሰሩ እና በሕብረት የሚያስቡ
ዜጎችን ትፈልጋለች።

ጌታ በነገር ሁሉ ማስተዋል ይስጠን!

አትፍራ!

ዲቮሽን 281/07 ሓሙስ ሰኔ 11/07
( ወንድም ጌታሁን ሓለፎም )

አትፍራ!

ዘፍ 15፡1 “ከዚህ ነገር በሗላ የእግዚአብሔር ቃል በራእይ ወደ አብርሃም መጣ እንዲህ ሲል አብርሃም ሆይ አትፍራ እኔ ለአንተ ጋሻህ ነኝ ዋጋህም እጅግ ታላቅ ነው ፡፡”

አባት ለልጁ ሁል ግዜ “አይዞህ እኔ አባትህ በህይወት እስካለሁ ድረስ ምንም ነገር አይገጥምህም ፤ ሁል ጊዜ ከጎንህ ነኝ ፤ በምንም ሁኔታ ውስጥ ብትሆን አትፍራ አትታወክ አትደንግጥ ካንተ ፈጽሞ አልለይህም ” ይለው ነበር ፡፡
ልጅም ከህጻንነቱ ጀምሮ “አይዞህ” የሚለውን እና የሚያበረታውን የአባቱን ድምጽ እየሰማ ስላደገ ፤ በምንም ሁኔታ ውስጥ ቢያልፍ ሳይፈራ እና ሳይደነግጥ በነጻነት ይወጣ እና ይገባ ነበር ፡፡ አንዳንድ ጊዜም ለሚገጥመው አስቸጋሪ ሁኔታ ቃል የገባለት አባቱ አጠገቡ እየተገኘ ይረዳው እና ለችግሩ ይደርስለት ስለነበረ ይበልጥ አባቱ ላይ መደገፍ
ሆነለት ፡፡

ከእለታት ባንዱ ቀን ግን እንዲህ ሆነ ፤ ለወትሮው ከአባቱ ጋር አንድ ላይ ያቁዋርጠው በነበረ ጥቅጥቅ ባለ ጫካ በኩል ብቻውን ማለፍ ግድ ሆነበት ፡፡ ጥቂትም እንደተጓዘ ከሩቅ አንድ የአንበሳ ደጎል እያገሳ ወደ እሱ ሲገሰግስ አየ፥ ብላቴናውም አካባቢውን ሲመለከት ከእሱ በቀር ሌላ ማንም ሰው የለም ፡፡ በልቡ ውስጥ ድንጋጤ እና ፍርሃት ሲሰማው ታውቀው ፡፡

ያንበሳውም ደጎል ይበልጥ እየገሰገሰ ወደሱ መቅረብ ጀመረ ፡፡ ብላቴናውም በፍርሃት ውስጥ እንዳለ በውስጡ የአባቱ ድምጽ አቃጨለበት “አይዞህ እኔ ከአንተ አልለይም ” ብላተናው ግን በዚህች ቅስበት ብዙ ጥያቄ ይመላለስበት ነበር “

ዛሬ ግን አባቴ ለምን ተለየኝ ፤ ለምን እንዲህ ባለ አስፈሪ ወቅት ያውም በዚህ በጫካ ለምን አባቴ ከኔ ተለየ አይዞህ አልለይህም ይለኝ አልነበረም ወይ ? ” እያለ የበለጠ ፍርሃት እና ድንጋጤ ውስጥ ገብቶ ያሰላስል ነበር፡፡

በዚህ መሃል እየገሰገሰ የመጣው አንበሳ ዘሎ እላዩ ላይ ሊከመርበት ሲል ከፍተኛ የፍንዳታ ድምጽ ሲሰማ እና አንበሳው መሬት ላይ ሲደፋ አንድ ሆነ፡፡ የተከሰተው ነገር ምን እንደሆነ ለማረጋገጥ ታላቅ ፍንዳታ ወደተሰማበት ስፍራ ዘውር ብሎ ሲመለከት አባቱን ከነ ጠበንጃው በታላቅ ፈገግታ ሆኖ ቆሞ ሲመለከተው አየ ፡፡

ብላቴናውም እየሮጠ አባቱ ላይ ተጠመጠመ ፡፡ እንዲህም አለው አባቴ አመሰግንህ አለሁ ለመጀመሪያ ጊዜ ዛሬ ከፍተኛ ድንጋጤ እና ፍርሃት ተሰምቶኝ ነበር አንበሳው ይበላኛል ብየ ተስፋም ቆርጨ ነበር እውነት
ነው እንደ ቃልህ ታምነህልኛል አለው ፡፡

ይገርማል በቃሉ የምንፈተንበት ቀን ለካ ይመጣል?

ዛሬስ ስንቶቻችን ነን ከገጠምን ችግር እና መከራ የተነሳ ፤ የነገራችን ፍጻሜ የመጨረሻው መራፍ ላይ የደረስን የመሰለን ? እግዚአብሔር ላንበሳና ለተኩላ አሳልፎ እስኪሰጠን ድረስ ዝም ብሎናል ትቶናል እረስቶናል ያልን ?

ስንቶቻችን ነን ጌታ በተለያየ ወቅት እና ጊዜ በቃሉ በነበያቱና ባገልጋዮቹ ተናግሮን ፤ አልጥላችሁም አልተዋችሁም ብሎን አሁን ግን ከምናልፍበት እና ከተጋረጠብን ፤ፈቀቅ አልል ካለን መከራ የተነሳ ተስፋ የቆረጥን ? እግዚአብሔር ተናግሮን ሲያበቃ ፊቱን ከኔ መልሶአል በአጠገቤ የለም የምንል ስንቶቻችን ነን ?

ወገኖቼ እሱ እግዚአብሔር ነው እና ፤ በሰማይ እና በምድር በባህሩና በጥልቁ የወደደውን የሚያደርግ አምላክ ነው እና፤ እርሱ የትንሳኤ አምላክ እና አባት ነው እና በውነት ጊዜው ይርዘም እንጅ ነገሮች አፍጥጠው ሊወርሱን ፤ ሊያሸንፉን አጠገባችን የተጋረጡ ይምሰለን እንጅ እግዚአብሔር እንደተናገረን እንዲሁ ይሆናል ፡፡

አብርሃም ስለ ልጅ መውለድ ጉዳይ ብዙ ዘመን ጠብቆ ጠብቆ 25 አመት በዘገየበት የተስፋ ቃል ምክኒያት በእግዚአብሔር ፊት እንዲህ አለ“ የቤቴ መጋቢ ደማስቆአዊው ኤሌዘር ሊወርሰኝ ነው ” አብርሃምን ድንገት
ድንጋጤ ጋረደው ፤ ፍርሃት ወረረው ፤ ለካስ ለዚህ ነበር ገና ከጅምሩ ከጧቱ እግዚአብሔር“አይዞህ” ብሎ የተናገረው መጽሓፍ ቅዱሳችን ላይ ወደ 365 ጊዜ የሚሆን በቀጥታ እና በተዘዋዋሪ አትፍራ የሚል ቃል ተጽፎ እናያለን ፡፡
እግዚአብሔር ለምንድን ነው ይህን ያህል አጠንክሮ “አትፍሩ” እያለ የሚናገረን ?“ በራሴ ጊዜ እመጣለሁ ፤ በራሴ ፈቃድ እና እቅድ እሰራለሁ ስለዚህ ነገር የዘገየ ቢመስልም ቃሌን እፈጽማለሁ እና እስከዚያው አይዟችሁ አትፍሩ ጠብቁ ” እያለን እኮ ነው ፡፡

እኔና እናንተ በተለያየ ችግር እና መከራ ውስጥ ስናልፍ ቀለል ባሉ ጉዳዮች ላይ እየታመነው ብዙ የሆነውን እርዳታ እየተቀበልን ብዙ ዘመን አልፈናል ፡፡ ነገር ግን የጠነከረ ወይም ካሰብነው በላይ ያገጠጠ ችግር ሲገጥመን ፍጹም መታመናችን ይጠፋል ፡፡ ነገር ግን ዛሬም ጌታ አትፍሩ አትደንግጡ እመጣለሁ እያለን ነው ፡፡

አሜን እግዚአብሔር ጋሻችን ነው እና አንፈራም !!!!

ይህንን መልእክት ሼር እና ላይክ በማድረግ ጌታን ያገልግሉ ፡፡ ጌታ ይባርካችሁ

'የውሸት እየኖርን' -- የእውነት እንሞታለን!

ዲቮሽን 280/07፥ ረቡዕ ሰኔ 11/07
(በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)

'የውሸት እየኖርን' -- የእውነት እንሞታለን!

ለዛሬው ዲቮሽን ርዕሴ ያደረግሁት አባባል፥ ታክሲ ውስጥ ተለጥፎ ያየሁት ነው! ይህን አባባል ማን እንደተናገረው የሚገልጽ ምንጭ ባላገኝም፥ ትልቅ አባባል መሆኑን ግን ደፍሬ እናገራለሁ፡፡

አዎ፥ የአንዳንዶቻችን ኑሮ የውሸት፥ የሽንገላ፥ የለበጣና የማስመሰል ኑሮ ነው፡፡ ነገረ ሥራችን ሲታይ፥ ከቤታችን ሌላ፥ ከቤት ውጭ ሌላ ነው፡፡ ከሰው ጋር ስንሆን ሌላ ለብቻችን ስንሆን ሌላ፡፡ የምናስበው ሌላ የምንናገረው ሌላ፡፡ የልባችን ሌላ፥ የከንፈራችን ሌላ! የሆዳችን ሌላ፥ የጥርሳችን ሌላ!

አዎይ የኛ ነገር፥ የኛ ነገርና እኛ ግራ ግብትኛ ነው! እየራበን እንግደረደራለን፥ አያማረን እንገፋለን፡፡ እየወደድን እየፈለግን የሆድ የአንጀታችንን እንሸሽጋለን፡፡ ከውስጥ እያለቀስን ከውጭ እንስቃለን፥ ከውስጥ እየሳቅን ከውጭ እናለቅሳለን፡፡ ውስጣችን ጮቤ እየረገጠ፥ በውጫችን ደረት እንደቃለን፡፡

አቤት የኛ ነገር፥ የኛ ነገርና እኛ፥ ግራ ግብትኛ! ንግግራችን ውስጠ ወይራ፥ ላይ-ላያችን ሌላ፥ ታህ-ታያችን ሌላ! አይጧ በበላች ደዋ፥ አህያ ፈርቶ ዳውላ፡፡ ፍየላችን ወዲህ፥ ቅምዝምዛችን ወዲያ፡፡

የአንዳንዶቻችን ሕይወት 'ፌክ' ይበዛበታል፡፡ ወዳጅ ከወዳጁ ጋር በሚኖረው ግንኙነት ፌክ፥ አንዱ ከሌላው ጋራ በሚኖረው ኅብረት ፌክ፥ በንግድ በገበያው ፌክ፥ በሱቅ በፋብሪካው ፌክ፥ በፖለቲካው መድረክ ፌክ፥ በየሐይማኖት ተቋሙ ፌክ፥ በየትምህርት ተቋሙ፥ በየቤተክርስቲያኑም ሆነ በየቤተክሲያኑ ፌክ፥ በየቦታው ሁሉ ፌክ ሞልቷል፡፡
ይህን ይህን ስናይ፥ "እውነትም "የውሸት እየኖርን" ያለ ይመስላል፡፡ እርግጥ ነው፥ የውሸት እየኖርን የውሸት አይሞትምና፥ የውሸት ብንኖርም የእውነት መሞታችን አይቀሬ ነው፡፡

ወገኖች ሆይ፥ የውሸት መኖር ይቅርብን! የእውነት ኑሮ መኖር ዛሬውኑ እንጀምር!

… ውሸትን አስወግዳችሁ፥ እርስ በርሳችን ብልቶች ሆነናልና እያንዳንዳችሁ ከባልንጀሮቻችሁ ጋር እውነትን ተነጋገሩ (ኤፌ 4፡25)

Tuesday, June 16, 2015

ያደረግነውን ሁሉ – ብናይ!



ዲቮሽን 279/07 ማክሰኞ፣ ሰኔ 9/07
(
በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)

ያደረግነውን ሁሉ – ብናይ!

እግዚአብሔርም ያደረገውን ሁሉ አየ፥ እነሆም እጅግ መልካም ነበረ…(ዘፍ 1፡31)።

እግዚአብሔር አምላክ የመፍጠር ሥራው ሒደት በእያንዳንዱ ዕለት ያደረገውን ሁሉ መለስ ብሎ ያይ ነበር፡፡ የስድስት ቀናቱን የመፍጠር ሥራውን ሁሉ ሲያጠናቅቅም፣ በአጠቃላይ ያደረገውን ሁሉ እንደ አየ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚመሰክርም፣ ­­‹‹እግዚአብሔር አምላክ ያደረገው ሁሉ እነሆ እጅግ መልካም ነበረ›› ይላል!

ወዳጆች ሆይ፣ የምናደርገውን ነገር ሁሉ መለስ ብለን እናያለን? በቀናት ውስጥ ያደረግነውን ሁሉ፣ በሣምንታት ውስጥ ያደረግነውን ሁሉ፣ በወራት ውስጥ ያደረግነውን ሁሉ፣ በዓመታት ውስጥ ያደረግነውን ሁሉ ወደኋላ ዞረን እንመለከታለን?

ወገኖች ሆይ፣ ያደረግነውን ነገር ሁሉ ወደኋላ መለስ ብለን ብንቃኝ፣ እንዴት እናገኘው ይሆን? ሥራችን ሲታይ፣ ክፉ ሆኖ ይገኝ ወይስ መልካም? ሁሉ ቻይ የሆነው አምላክ እንኳን ያደረገውን ሁሉ ካየ፥ እኛስ ይልቁንም እንዴት አብልጠን ሥራችንን አንገመግም?

ወገኖች ሆይ፣ እግዚአብሔር አምላክ ያደረገውን ነገር በእያንዳንዲቱ ቀን መለስ ብሎ ካየ፣ እንዲሁም በሥራው ማጠናቀቂያ ላይ አጠቃላይ ግምገማ ካደረገ፣ እኛስ ደካሞችና ልዩ ልዩ ሸክም የከበደብን የሰው ልጆች ሁሉ፣ በየዕለቱና በየጊዜው ያደረግነውን ነገር ሁሉ ወደኋላ መለስ ብለን ብንቃኝ፣ ሥራችንንና ራሳችንን መመርመር ምንኛ ያስፈልገን ይሆን?

Sunday, June 14, 2015

አዋቂ!!!!

ዲቮሽን 278/07 ሰኞ፣ ሰኔ 8/07
(
በእህት ማርታ ሲሳይነህ)

አዋቂ!!!!

እግዚአብሔር አዋቂ ነውና” 1 ሳሙ 23

እውቀት ያለ ገደብ፣ በሰኮንዶች ሽርፍራፊ ዓለምን እያደረሰበት ያለበት ጊዜ ቢኖር ይህ የኛ ዘመን ነው። በአንድ መንገድ እንገድበው፣ ብንል እንኳን በሌላ መንገድ ይፈሳል። እውቀት እንደ ጅረት ወንዝ የሚፈስበት ዘመን ማለት ይህ ነው። እያንዳንዳችንም ብንጠየቅ፣ አዋቂወች ነን የምንልበት ዘመን ነው-አሁን። ሰው ህይወቱን በእቅድ ለመምራት፣ ዘመናዊ አካሄዶችን ወደ ተግባር የሚለውጥበት ዘመን ነው- አሁን። ከእያንዳንዱ ደቂቃ እስከ ዓመታት ድረስ ለህይወታችን እቅድ እናወጣለን- በዚህ ዘመን። እንደ ካሌንደራችን ካልሔድን ደግሞ፣ እንከፋለን፣ ወይም ሁሉም ነገር የተበላሸ ይመስለናል።

የእግዚአብሔር እውቀት ግን ግሩም ነው። ለኔ እና ለእናንተ ያለው የዘላለም እቅዱና እውቀቱ አንዳንዴ፣ እኛ ምን ያህል ሞኞች እንደሆንን እና የጌታን የእውቀት ፍጽምና ልንመረምረው አለመቻላችን ህይወታችንን ምን ያህል፣ እንደሚያውከው ስንረዳ፣ ወየው! የእግዚአብሔርን ሀሳብ ቀድሜ ባወቅሁኝ ኖሮ እኮ እንዲህ አልኳትንም ነበር እንላለን።

እግዚአብሔር፣ ገና ሳንወለድ ጀምሮ ያለውን ነገር ያውቃል፤ ነገ ምን እንደሚገጥመንም ያውቃል፣ ከዓመታት በኋላም ምን ላይ እንደምንደርስ ያውቃል። ያውቃል። በእርግጥ ያውቃል!!!!

ከእሱ እውቀት ውጭ የሆነ አንዳችም ነገር የለምና፣ ወገኖቼ ሆይ ዛሬ፣ ለኔም ለእናንተም፣ ለሁላችንም ማረፍ ይሁንልን። ብቻ በእግሩ ሥር የሚያስጨንቀንን ሁሉ እየጣልን እንሂድ። እርሱ አዋቂ ነውና፣ ሀሳቡም አይመረመርምና!

አባትዬ፣ እረፉ እኔም አምላክ እንደሆንኩ እወቁ ያልከን ወዳጃችን ሆይ፣ ለዘላለም በክንፎችህ ጥላ ሥር ማረፍ ይሁንልን። ወደ እረፍትህ አስገባን። አዋቂ ነህና፣ ከመቅበዝበዝ ህይወት አውጣን። ውድየ፣ ሰምተህኛልና ተባረክ። እፎይ!!!!
ትምህርቱ ጠቅሞዎታል? እንግዲያውስ እባክዎ፣ ላይክ እና ሼር፣ ኮሜንትም ያድርጉ።