ዲቮሽን 282/07፥ አርብ፥ ሰኔ 12/07
(በወንድም አበባዬ )
ሕብረት እና ስኬት
(በወንድም አበባዬ )
ሕብረት እና ስኬት
" አንዱም አንዱን ቢያሸንፍ ሁለቱ በፊቱ ይቆማሉ፤ በሦስትም የተገመደ ገመድ ፈጥኖ አይበጠስም። "(መጽሐፈ መክብብ 4:12)
ከ ኢየሱስ ጋር አዲስ ግንኙነት በጀመርኩባቸው የመጀመሪያ
ዓመታት የመንፈሳዊ ዕድገት ሶስት መሰረቶች ተብየ
ከተማርኳቸው ነገሮች ውስጥ አንዱ ሕብረት ነበር። ( ሌሎች
ሁለቱ ፀሎት እና የእግዚያብሄር ቃል ናቸው) ድስት በሦስት
ጉልቻ እንደሚቆም አማኝም ያለ እነዚህ ሦስቱ አይቆምም
ሲል መንፈሳዊ አባቴ ያሰተማረኝን አልረሳውም። በቃሉ እና
በፀሎት የበረታን ብንሆንም ከ ሌሎች አማኞች ጋር ጤናማ
ሕብረት ከሌለን ዕድገታች ምልዑ አይሆንም።
ይህ ጊዜ ከመቸውም ጊዜ በላይ ግለኝነት የተንፀባረቀበት
ጊዜ ነው። ግለኝነት እራሱ አንዱ የድህረ ዘመናዊነት
አስተሳሰብ ውጤት ነው። ሰዎች ከራሳቸው እና የራሳቸው
ከሆነው በላይ ለማንም የማይጨነቁ ይመስላል።
ለስኬታቸውም ሆነ ለውድቀታቸው የሌሎች ሚና እዚህ ግባ
የማይባል እንደሆነ የሚስቡ ይመስላል። ይህ ከመፅሐፍ
ቅዱሱ የሕይወት ፍልስምና ጋር ይጋጫል።
ሕብረት የክርስትና ሕይወት አንዱ ቁልፍ ነው። ለመንፈሳዊ
ሕይወታችንም ዕድገት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ግልፅ ነው።
ከምንም በላይ ግን ከስኬት እና ውጤታማነት ጋር ከፍተኛ
ቁርኝት አለው።
በሕይወታችን እና በአገልግሎታችን እንዲሳካልን ካስፈለገ
ጤናማ ሕብረት ሊኖረን ያስፈልጋል። እኛው በእኛው ለኛው
የሆነ ህይወት እና አግልግሎት የለም። በቤተክርስቲያንም
ሆነ በሌሎች ተቋማት በሚኖረን ተሳትፎ በሕብረት ልናምን
ይገባል። አንደኛው ዘርፍ ከሌላው ጋር በሕብረት ተቀናጅቶ
ካልሰራ ስኬት ላይ አይደረስም። በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ
የተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች ተናበው እና እርስ በርስ
ተደጋግፈው በሕብረት ሲሰሩ የሚያሰማ ውጤት ይመጣል።
አሁን አንዳንድ ቦታዎች ላይ እንደሚታየው አንዱ የአንዱን ስራ
በሚያንቋሽሽበት እና በሚያፈርስበት ሁኔታ ግን ለውጥ
ሊመጣ አይችልም። "አንድ ሰው አስቦ በአንድ በሬ ስቦ"
እንደሚባለው ማለት ነው።
ወገኖቼ እየተፈታተነን ያለውን ግለኝነት ልናሸንፈው ይገባል።
ለሕይወቴ እና ለስኬቴ ሌላው ወንድሜ ያስፈልገኛል
የሚለውን የቀደመ አስተሳሰብ ልናዳብር ይገባል። በግላችን
ምንም እንኳን ጥቂት ርቀት ልንሄድ የምንችል ቢሆንም የትም
ደረጃ ልንደርስ ግን እንደማንችል ልናምን ይገባል።
አሁን ቤተክርስቲያን ልዩነታቸውን አስፈተው በመቀናናት እና በ
መገፋፋት የሚነካከሱ ሳይሆን በ ጋራና በጤናማ ሕብረት
የሚሰሩ የተናበቡ አገልጋዮችንና ኣና አማኞችን ትፈጋለች።
የራሳቸውን ምኞት አረፋ እየደፈቁ በእኔነት መንፈስ ሕዝቡን
ግራ የሚያጋቡ መንጋውን የሚበትኑ ሳይሆን ቀርበው በፍቅር
የሚያቅፉትን ሰፊ ትክሻ ያላቸው እና በሕብረት የሚያምኑ
መሪዊችን ትፈልጋለች። አሁን አገራችን በራሳቸው የብልፅግና
ምኞት ሰክረው ሁሉን እንደ ማግኔት ወደራሳቸው የሚስቡ
ስግብግቦችን ሳይሆን በጋራ የሚሰሩ እና በሕብረት የሚያስቡ
ዜጎችን ትፈልጋለች።
ጌታ በነገር ሁሉ ማስተዋል ይስጠን!
ከ ኢየሱስ ጋር አዲስ ግንኙነት በጀመርኩባቸው የመጀመሪያ
ዓመታት የመንፈሳዊ ዕድገት ሶስት መሰረቶች ተብየ
ከተማርኳቸው ነገሮች ውስጥ አንዱ ሕብረት ነበር። ( ሌሎች
ሁለቱ ፀሎት እና የእግዚያብሄር ቃል ናቸው) ድስት በሦስት
ጉልቻ እንደሚቆም አማኝም ያለ እነዚህ ሦስቱ አይቆምም
ሲል መንፈሳዊ አባቴ ያሰተማረኝን አልረሳውም። በቃሉ እና
በፀሎት የበረታን ብንሆንም ከ ሌሎች አማኞች ጋር ጤናማ
ሕብረት ከሌለን ዕድገታች ምልዑ አይሆንም።
ይህ ጊዜ ከመቸውም ጊዜ በላይ ግለኝነት የተንፀባረቀበት
ጊዜ ነው። ግለኝነት እራሱ አንዱ የድህረ ዘመናዊነት
አስተሳሰብ ውጤት ነው። ሰዎች ከራሳቸው እና የራሳቸው
ከሆነው በላይ ለማንም የማይጨነቁ ይመስላል።
ለስኬታቸውም ሆነ ለውድቀታቸው የሌሎች ሚና እዚህ ግባ
የማይባል እንደሆነ የሚስቡ ይመስላል። ይህ ከመፅሐፍ
ቅዱሱ የሕይወት ፍልስምና ጋር ይጋጫል።
ሕብረት የክርስትና ሕይወት አንዱ ቁልፍ ነው። ለመንፈሳዊ
ሕይወታችንም ዕድገት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ግልፅ ነው።
ከምንም በላይ ግን ከስኬት እና ውጤታማነት ጋር ከፍተኛ
ቁርኝት አለው።
በሕይወታችን እና በአገልግሎታችን እንዲሳካልን ካስፈለገ
ጤናማ ሕብረት ሊኖረን ያስፈልጋል። እኛው በእኛው ለኛው
የሆነ ህይወት እና አግልግሎት የለም። በቤተክርስቲያንም
ሆነ በሌሎች ተቋማት በሚኖረን ተሳትፎ በሕብረት ልናምን
ይገባል። አንደኛው ዘርፍ ከሌላው ጋር በሕብረት ተቀናጅቶ
ካልሰራ ስኬት ላይ አይደረስም። በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ
የተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች ተናበው እና እርስ በርስ
ተደጋግፈው በሕብረት ሲሰሩ የሚያሰማ ውጤት ይመጣል።
አሁን አንዳንድ ቦታዎች ላይ እንደሚታየው አንዱ የአንዱን ስራ
በሚያንቋሽሽበት እና በሚያፈርስበት ሁኔታ ግን ለውጥ
ሊመጣ አይችልም። "አንድ ሰው አስቦ በአንድ በሬ ስቦ"
እንደሚባለው ማለት ነው።
ወገኖቼ እየተፈታተነን ያለውን ግለኝነት ልናሸንፈው ይገባል።
ለሕይወቴ እና ለስኬቴ ሌላው ወንድሜ ያስፈልገኛል
የሚለውን የቀደመ አስተሳሰብ ልናዳብር ይገባል። በግላችን
ምንም እንኳን ጥቂት ርቀት ልንሄድ የምንችል ቢሆንም የትም
ደረጃ ልንደርስ ግን እንደማንችል ልናምን ይገባል።
አሁን ቤተክርስቲያን ልዩነታቸውን አስፈተው በመቀናናት እና በ
መገፋፋት የሚነካከሱ ሳይሆን በ ጋራና በጤናማ ሕብረት
የሚሰሩ የተናበቡ አገልጋዮችንና ኣና አማኞችን ትፈጋለች።
የራሳቸውን ምኞት አረፋ እየደፈቁ በእኔነት መንፈስ ሕዝቡን
ግራ የሚያጋቡ መንጋውን የሚበትኑ ሳይሆን ቀርበው በፍቅር
የሚያቅፉትን ሰፊ ትክሻ ያላቸው እና በሕብረት የሚያምኑ
መሪዊችን ትፈልጋለች። አሁን አገራችን በራሳቸው የብልፅግና
ምኞት ሰክረው ሁሉን እንደ ማግኔት ወደራሳቸው የሚስቡ
ስግብግቦችን ሳይሆን በጋራ የሚሰሩ እና በሕብረት የሚያስቡ
ዜጎችን ትፈልጋለች።
ጌታ በነገር ሁሉ ማስተዋል ይስጠን!
No comments:
Post a Comment