Thursday, January 22, 2015

ዝቅ፣ ከፍ – ዝቅ፣ ከፍ፣ ከፍ!

ዲቮሽን .134/07     ሐሙስጥር 14/07 ..
(በመጋቢ ተስፋሁን ሐጢያ)


ዝቅ፣ ከፍ – ዝቅ፣ ከፍ፣ ከፍ

እግዚአብሔር ድሀ ያደርጋል፥ ባለጠጋም ያደርጋል ያዋርዳል፥ ደግሞም ከፍ ከፍ ያደርጋል(1 ሳሙ 2፡7)።

ሰዎች ነንና፣ አግኝተን ስናጣ፣ ወጥተን ስንወርድ፣ ከብረን ስንዋረድ፣ ስቀን ስናለቅስ እጅግ ይከፋናል፡፡ ሰዎች ነንና፣ የሞላው ሲጎድል፣ የሰፋው ሲጠብብ፣ እጅግ ይከፋናል፡፡

ወገኖች ሆይ፣ ከላይ የቀረበው ጥቅስ ልዑል የሆነው እግዚአብሔር፣ በሰማይ ሠራዊት፣ በምድርም ላይ በሚኖሩ መካከል እንደ ፈቃዱ የሚያደርግ መሆኑን፣ እጁንም የሚከለክላት ወይም ‹‹ምን ታደርጋለህ?›› የሚለው የሌለው መሆኑን ጮኾ ይናገራል!

ወገኖች ሆይ፣ ካላይ የተነበበው ጥቅስ፣ እጁ ተይዞ ‹‹ምን ታደርጋለህ?›› የማይባለው ይኼ ልዑል አምላክ፣ በሰማይ ሠራዊት፣ በምድርም ላይ በሚኖሩ መካከል የፈቀደውን ነገር እንዴት እንደሚያደርግ ፎርሙላ ያቀርባል፡፡

ወገኖች ሆይ፣ የእግዚአብሔር ፎርሙላ እንዲህ ይነበባል፡፡ ድሀ (ዝቅ) ያደርጋል፣ ባለጠጋም (ከፍ) ያደርጋል – ያዋርዳል (ዝቅ)፥ ደግሞም (ከፍ ከፍ) ያደርጋል!

ጆሮ ያለው ይስማ!  ሁሉን ቻይ እግዚአብሔር፣ እርሱ እንደወደደ በሰማይ ሠራዊት፣ በምድርም ላይ በሚኖሩ የሰው ልጆች መካከል ዝቅ፣ ከፍ – ዝቅ፣ ከፍ፣ ከፍ ያደርጋል
እደግመዋለሁ፣ ጆሮ ያለው ይስማ! የእግዚአብሔር ፎርሙላ እንዲህ ይነበባል – እግዚአብሔር ዝቅ፣ ከፍ – ዝቅ፣ ከፍ፣ ከፍ ያደርጋል

ወገኖች ሆይ፣ በሕይወታችን ጉዞ መውረድና መውጣት መውደቅ፣ መነሳትና መክበር ሁልጊዜም ይኖራል! ማልቀስና መሳቅ ማዘን፣ መጽናናትና መደሰት  ሁልጊዜም ይኖራል! ማጣትና ማግኘት መዝራት፣ ማጨድና መብላት ዘወትር ይኖራል! ውርደትና ክብር ስደት፣ እረፍትና መንገሥ ዘወትር ይኖራል!

ታውቃላችሁ፣ መደኽየት፣ መበልጸግ መበተን፣ መልቀምና ማባዛት ዘወትር ይኖራል፡፡ ስለሆነም፣ አግኝተን ስናጣ፣ አጥተንም ስናገኝ የእግዚአብሔርን ፎርሙላ በጭራሽ አንርሳ! ያገኘም – ያጣና፣ ያጣም – ያገኝና፣ የሆነች ቦታ ላይ – መገናኘት አለና፣ የእግዚአብሔርን ፎርሙላ ማስታወስ ይገባል!

ወገኖች ሆይ፣ የእግዚአብሔር ፎርሙላ እንዲህም ይቀርባል – እግዚአብሔር የኃያላንን ቀስት ሰብሮ ደካሞችን በኃይል ያስታጥቃል። የጥጋበኞችን መሶብ ደፍቶ የረሀብተኞችን ቡሀቃ ይሞላል! ብዙ የወለዱትን አድክሞ መካኖቹን በልጅ ይባርካል! የእግዚአብሔር ፎርሙላ –ይገድላል ያድናል፣ ሲኦል ያወርዳል፥ ያወጣል!

ስለዚህ፣ የቅድስት ሐና ቅኔ እንዲህ ይዘረፋል – እግዚአብሔር አዋቂ ነውና፥ አንታበይ፣ በኩራት አንናገር! እግዚአብሔርም ሥራን የሚመዝን ነውና፥ ከአፋችን የኵራት ነገር አይውጣ! እግዚአብሔር ዝቅ፣ ከፍ – ዝቅ፣ ከፍ፣ ከፍ ያደርጋልና
-----
ትምህርቱ ጠቅምዎታል? እንግዲያውስ ላይክ ያድርጉ፡፡ ጌታ ይባርክዎ!

--------------------------------

‹‹የወንጌላዊ እጮኛ›› አዲስ መጽሐፍ፣ በገበያ ላይ ውሏል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በ0911 678158 ወይም 0911 813092 ይደውሉ፡፡

Thanks for Nothing!

Tesfahun Weekly (4/2015)
(By Pr. Tesfahun Hatia)

Thanks for Nothing!

Yesterday (January 21/15), I was visiting one of the teaching hospitals in Addis Ababa with a friend. While we were sitting at one of the corridors, I saw a Hemodialysis room in front of us. Hemodialysis is an artificial procedure of removing waste from the kidneys using plastic tubes. This is a room where patients who cannot remove their waste in a natural way go and get assistances.

Often times, we seem to be covered with blindness for there are many things around us but we get zero lessons. Sometimes, we only focus on ourselves and fail to see the external factors that are full in wisdom.

Dear friend, is there anything holding you back because there is no reason to give thanks to the Lord? Look around and you can find some. If you look around and still not able to see pictures, just give thanks to the Lord for nothing!

Be careful for nothing; but in everything by prayer and supplication with thanksgiving let your requests be made known unto God (Phil 4:6).

_____________

Tesfahun is an educator, Pastor and writer. He has a daily devotion on facebook and blog. He can be reached through (email: tesfahun.et@gmail.com and www.facebook.com/tesfahun.hatia and www.blogger/Tesfahun Hatia)