ዲቮሽን ቁ.8/2007 ሐሙስ፥ መስከረም 8/2007 ዓ.ም.
(በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)
(በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)
አንዱም
ለአንዱ
እንዲህ
አለው፥
ያ ባለ ሕልም ይኸው
መጣ፡፡
አሁንም
እንግደለውና
በአንድ
ጉድጓድ
ውስጥ እንጣለው…ከሕልሞቹም የሚሆነውን
እናያለን
(ዘፍ 37፡20)
ጠላታችን
ዲያብሎስ
ባለ ራዕዮችን ለማጥፋት ዘወትር
እንደጣረ
ነው፡፡
በነፍሳቸው
ላይ በመሸመቅ፥ ጉድጓድ በመቆፈር፥
ልዩ ልዩ መሰናክሎች በማስቀመጥ፥
ክፉ ነገሮችን ሁሉ በማድረግ
እቅዱ እንደሚሳካለት ተስፋ ያደርጋል፡፡
ነገር ግን ጠላታችን ሁሌም
እንዳፈረና
እንደተዋረደ
ነው! እግዚአብሔር ሕዝቡን አይጥልምና
እቅዶቹ
ሁሉ እየከሸፉበት ውርደት እንደተከናነበ
ነው፡፡
ጠላት በባለራዕዮች ላይ የሚያስበው
ክፉ ምኞት ሁሉ ወዳልተጠበቀ
የምስራች
እንደተቀየሩበት
ነው፡፡
ሞትን ሲያቅድ ወደ ሕይወት
ይበወዝበታል፡፡
የውርደት
ቅዠቱ ወደ ክብር ይለወጥበታል፡፡
የባርነት
እቅዱ ወደ ዙፋን ይቸኩልበታል፡፡
ረሀብ በጥጋብ፥ ለቅሶ በዝማሬ፥
ሐዘን በደስታ ይተካበታል!
ባለራዕይ
አይሞትም!
የሞት ድግስ ቢደገስበት፥ ነጋሪት
ቢጎሰምበት፥
እምቢልታ
ቢነፋበት
…ባለራዕይ
አይሞትም!
ጠላት በባለራዕይ ላይ ከበሮ
ቢደልቅ፥
ጸናጽል
ቢያንሿሿ፥
ዋሽንት
ቢነፋ፥
በገና ቢደረድር፥ ጥሩንባ ቢነፋ፥
ፉከራ ቢያበዛ፥ ጉራውን ቢነዛ…
ባለራዕይ
አይሞትም፥
አይጠፋምም!!
ጠላት ባለራዕዮችን ከምድር ላይ
ሊያጠፋ
የሚፈልግበት
ምክንያቱ
ለምን ይመስላችኋል? አንድ ሺህ
አንድ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡
ጥቂቶቹን
ላንሳ፡፡
ባለራዕዮች
ከጠፉ ራዕይ ይጠፋል፡፡ ራዕይ
ከጠፋ ደግሞ ሕዝብ መረን
ይሆናል፡፡
ባለራዕዮች
ከምድር
ላይ ከጠፉ ምድር ራሷ
በቀላሉ
ትጠፋለታለች!
ይህ እንዳይሆን ባለራዕይ እይጠፋም፥
አይሞትምም!!
(ይህን
ዕለታዊ
ዲቮሽን
ላይክ ያድርጉ፥ ለወዳጅ ጓደኞችዎም
ያስተላልፉ)
No comments:
Post a Comment