ዲቮሽን 346/07፥ አርብ፥ ነሐሴ 16/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
ዘፀአት ሆነልን!!!!!
ልክ አራት መቶ ሠላሳው ዓመት በተፈጸመ ዕለት የእግዚአብሔር ሰራዊት ሁሉ ግብፅን ለቆ ወጣ። ዘፀ 12፡41
እፎይ፣ ነፃነታችን እኮ እውነት አይመስልም አይደል? ግን ሆነ።
እስከዛሬም የቆየነው የአምላካችን ልክ፣ ማንነት፣ ወርድና ስፋት፣ ለምድር ሁሉ መታወቅ ስላለበት፣ እንዲሁም የጠላቶቻችን በኩሮች ሁሉ መቀሰፍ ስላለባቸው ነው። እንጂ ግብፅን በዝብዘን እንደምንወጣማ የታወቀ ጉዳይ እኮ ነው!!! (ዘፀ 3፡22)።
ታዲያ፣ ዛሬ ዘፀአት ሆነልን!!
ያ፣ እግዚአብሔርን አላውቅም፣ እስራኤልንም አለቅም እያለ ሲፎክር የነበረው፣ ፈርዖናችን (እያንዳንችን እኮ ስንት ዓይነት ፈርዖንና ሠራዊቱ ሲገዛን ኖሯል! ዝርዝሩን እናንተ ሙሉበት) የኤልሻዳዩ ሰዓት ሲደርስ፣ እናንተ እስራኤላውያን ከሕዝቤ መካከል ውጡ! በጠየቃችሁት መሠረት እግዚአብሔርን አምልኩ ብሎ ጭራሽ ሸኘን እኮ!
ድሮስ፣ የእኛ ጌታ በኩር በኩሩን እያነቀ ቋ፣ ቋ፣ ቋ፣ ሲጥ ሲያደርግበት ወዶ ነው የሚለቀን! እኛም ዘመናችንን ሁሉ እግዚአብሔርን እናመልካለን። ልጆቻችን፣ የልጅ ልጆቻችንም ሁሉ ሲጠይቁን፣ “ከባርነት ምድር ከግብፅ እግዚአብሔር በሐያል ክንዱ አወጣን። ፈርዖን እኛን አለቅም ብሎ ልቡን ባደነደነ ጊዜ፣ ከሰው ጀምሮ እስከ እንስሳ ድረስ በኩር ሆኖ በግብፅ የተወለደውን ሁሉ እግዚአብሔር ገደለው።” እያልን እንመሰክራለን!!!
ዐይኖቼ የባልንጦቼን ውድቀት አዩ፣ ጆሮዎቼም የክፉ ጠላቶቼን ድቀት ሰሙ። መዝ 92:11
---------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 20 ቀን ቀርቶታል
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 20 ቀን ቀርቶታል
No comments:
Post a Comment