ዲቮሽን 342/07፥ ማክሰኞ፥ ነሐሴ 12/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
ጌታ ነዋ!!!!!!
ስለዚህ እንደሞተ ሰው ከሚቆጠር ከዚህ ከአንድ ሰው፣ እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛና እንደ ባህር ዳር አሸዋ ተቆጥሮ የማያልቅ ዘር ተገኘ። ዕብ 11፡12
የአብርሐም የአንድ ልጅ ጥያቄ ለዘመናት ከእግዚአብሔር ጋር ሲያጨቃጭቀው ቆይቷል። አይ እግዚአብሔር! እንዴት ድንቅ ነው! ዔሊኤዘር ይወርሰኛል እያለ ሲፈራ የነበረው አብርሐም፣ የትውልድ ሁሉ አባት ለመሆን በቃ። ተረት አይመስልም? ግን እውነት ነው!
እግዚአብሔር እንዲህ ነዋ! እግዚአብሔርን ምንም ነገር አያስፈራውም። ሳይንስ አያስፈራውም፣ እድሜ አያስፈራውም፣ መልክዓምድራዊ አቀማመጥ አያስፈራውም፣ ሞት አያስፈራውም፣ መንግስታት አያስፈሩትም፣ ..እሱ ግን ሥራውን በራሱ ጊዜ ይሠራል! ከለመንነውም ከጠየቅነውም በላይ ማድረግ ይችላል።
ታዲያ ዛሬ በሰውም በእናንተም ዓይን የሞተው ነገር ምንድን ነው? የተቀበረውስ አልአዛር የትኛው ነው? እግዚአብሔር እልፍ ያለ ነገር በእያንዳንዳችን ሕይወት ላይ አይቷል። መንፈስቅዱስን ዝም ብላችሁ አመስግኑት። እወድሐለሁ በሉት።
አምላክ ሆይ፣ ለእኔ ያለህ ሐሳብ እንዴት ክቡር ነው። ቁጥራቸውስ እንደምን በዛ! ብቆጥራቸው ከአሸዋ ይልቅ ይበዛሉ። መዝ 139፡17
---------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 24 ቀን ቀርቶታል
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 24 ቀን ቀርቶታል
No comments:
Post a Comment