Saturday, August 22, 2015

ዮሴፍ በሕይወት አለ!!!!!!!

ዲቮሽን 344/07፥ ሐሙስ፥ ነሐሴ 14/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)

ዮሴፍ በሕይወት አለ!!!!!!!

ዮሴፍ የላከለትን ሠረገላዎች ሲያይ የአባታቸው የያዕቆብ መንፈስ ታደሰ። ከዚያም እስራኤል፣ “ልጄ ዮሴፍ በሕይወት አለ፣ ከመሞቴ በፊት ሂጄ ልየው”አለ። ዘፍ 45፡28

በጣም የምትፈልጉት ነገር ሞቷል ብሎ ጠላት መርዶ የነገራችሁ ምንድን ነው? ለመሞቱም ጠላት ምልክት በደም ነክሮ ያረጋገጠላችሁ ነገር ምንድነው? እናንተም ጌታ የተናገረኝ ነገር እንዴት ሳይሆን ቀረ እያላችሁ በስብራት ትኖራላችሁ አይደል? ነገሩ ትዝ ሲላችሁ ስታለቅሱ ስንት ዓመት ሆናችሁ ይሆን?

የሰማነው መርዶ ባለማረጋገጫ ስለሆነ፣ ይህማ የልጄ እጀ ጠባብ ነው፤ ክፉ አውሬ በልቶታል በእርግጥም ዮሴፍ ተበጫጭቆአል፣ እያልን ስንት ዓመታት አለፉ! ጠላትም ስብራታችንን እያየ ሲዘባነንብን፣ ብዙ ዓመታት ተቆጠሩ አይደል? በመጨረሻም፣ በሐዘን እንደተኮራመትን ወደ መቃብር እንወርዳለን ብለን ደመደምን አይደል! ስንት ውሸትን በማስረጃ እያስደገፈ ሲያስደንግጣችሁ እና ሲያባንናችሁ ኖረ አይደል!

አሁን አንገት የመድፊያው ጊዜ የጠላት እንጅ የእኛማ አይደለም! አሁን ጠላት ከነዘርማንዝሩ ለቅሶ ይቀመጥ፣ ምክንያቱም የተቀበረው የጠላት ልጅ እንጅ የእኛ ዮሴፍማ በሕይወት አለ። ዮሴፋችን በሕይወት አለ።

ዛሬ እግዚአብሔርን እንዲህ እንለዋለን፣
---------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 22 ቀን ቀርቶታል

No comments:

Post a Comment