Saturday, August 22, 2015

በማትረፍረፍ የታወቀ!!!!

ዲቮሽን 345/07፥ አርብ፥ ነሐሴ 15/07 ዓ/ም 
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)

በማትረፍረፍ የታወቀ!!!!

ፊትህን አያለሁ ብዬ አላሰብሁም ነበር። እነሆም እግዚአብሔር ዘርህን ደግሞ አሳየኝ። ዘፍጥ 48፡ 11
የእኛ እግዚአብሔር በማትረፍረፍ የታወቀ ነው። የተትረፈረፈ ሰላም፣ የተትረፈረፈ ይቅርታና ምህረት፣ የተትረፈረፈ ባለጸግነት እና ሕይወት የሚገኘው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ብቻ ነው።
ያዕቆብ፣ ስለ ሞተ ልጁ ሲያለቅስ ዓመታት ተቆጠሩ። ያ ብላቴናው ዮሴፍ ባይን ባይኑ እየሄደበት ብዙ ተክዟል። እንዲያው በቀበርኩት፣ ሬሳውን እንኩዋን ባየሁት እያለ! እንዲያው የልጄን ቀን በሰጠኝ እያለ ያዕቆብ ሲያለቅስ፣ ማስደነቅ የሚያውቀው የእኛ እግዚአብሔር ግን፣ በራሱ ሰዓት እና ጊዜ ከች አለ።
ያውም ዮሴፍ ሲመጣ መለመላውን ሆኖ አይደለም። ለተራበች ምድር ብቸኛ ተስፋ ሆኖ!!!! የልጁን ዓይን ብቻ ለማየት ምንም የተስፋ ጭላንጭል ያልነበረው ያዕቆብ፣ ዕልፍ ብሎ፣ የዮሴፍንም ልጆች አየ: ኤፍሬምና ምናሴን!!!!!!! እሥራኤል አያት ሆነ እኮ ነው እያልኩዋችሁ ያለሁት!!!!! እረ አለ ገና!!!!
ያዕቆብ የልጁን ሬሳ እንኩዋን ቢያገኝ ደስታው ወደር አልነበረውም። ደመ-ከልብ ሆኖ የቀረ መስሎት እኮ ነው በሀዘን ሲብሰለሰል የኖረው!!!! ወይም ደግሞ አካሉ ጎድሎ፣ ወይ ጎስቁሎ ቢመጣለት፣ እጅግ ይደሰት ነበር።
ሆኖም ግን.....
ዮሴፍ ባለፀጋ፣ ሀገረ ገዥ ሆኖ፣ አግብቶ ወልዶ፣ ተትረፍርፎ መጣ።
እግዚአብሔር ነዋ!!!!!!!
አንድ ሲጠየቅ አሥር እጥፍ አድርጎ በመስጠት የታወቀ የእኛ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ኦ መንፈስ ቅዱስ ሆይ፣ እንዴት ግሩም ነህ!!!!!
እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል መጠን ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው (ኤፌ 3: 20) ለእግዚአብሔር አምልኮ እና ስግደት፣ ክብር ይገባዋል።
---------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 21 ቀን ቀርቶታል

No comments:

Post a Comment