Monday, August 17, 2015

ትልቅ ለማኙ /Asker of Big

ዲቮሽን 341/07፥ ሰኞ፥ ነሐሴ 11/07 ዓ/ም 
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)

ትልቅ ለማኙ /Asker of Big

ለምነኝ መንግስታትን ለርስትህ፣ የምድርንም ዳርቻ ግዛት እንዲሆንህ እሰጥሀለሁ። መዝ 2፡8

ህፃን ልጅ አባቱ/እናቱ ሁሉን ማድረግ የሚችሉ ነው የሚመስለው። ስለዚህ ሲጠይቅ አይሳቀቅም። ወላጆቼ ገንዘብ ወይ ዓቅም ላይኖራቸው ይችላል ብሎ አያስብም። የፈለገውን ይጠይቃል። ያምናቸዋል፤ ይመካባቸዋል። ይኮራባቸዋል።

የእኛ እግዚአብሔርስ?

አሁን እግዚአብሔርን አይተነዋል። ቀምሰነዋል። ዳስሰነዋል። አይደለም እንዴ?

ታዲያ ጥያቄያችንም ልክ እንዳየው ሰው ነው። አሁን ደጀሰላም ላይ ተቀምጠን ምጽዋትን አንለምንም። አሁን አሥር እና አምስት ሳንቲም ብቻ አንለምንም። አሁን ከህመማችን ብቻ እንዲፈውሰን አንለምንም። አሁን ከኤኮኖሚ ድህነት ብቻ ነጻ እንድንወጣ አንለምንም። አሁን የትዳር አጋር ብቻ አንለምንም። አሁን መኖሪያ ቤት ወይ መሰል ነገር ብቻ አንጠይቅም።

አሁን ልመናችን ተቀይሯል። ዋናውን አግኝተነዋላ!!!! እሱም እኮ፡ ለምነኝ መንግስታትን ለርስትህ፣ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሀለሁ ብሎናል። ስለዚህ It is time to exercise our child right. ቀላል እንለምናለን እንዴ?! እንጮሀለን እንጂ!! እ--ን--ለ--ም--ና--ለ--ን!! አህዛብን ለቤተክርስትያን፣ የምድርንም ዳርቻ ለግዛታችን የሚሰጠውን፡ እሱን እግዚአብሔርን እንለምናለን። አናቋርጥም። እንጮሐለን!! ሰጭውን ላልከበደው፣ እኛን ለማኞቹን ምን አሳቀቀን ወገኖቼ? በተራው እዚያው ጠላታችን ይሳቀቅ እንጂ!!

ዋ! ኋላ መንግስተ ሰማያት ላይ ሔዳችሁ ከመቆጨት፣ ይሔ ሁሉ ለኔ ነበር እንዴ? ከማለት፣ ዛሬ የምትፈልጉትን ሁሉ በስሙ ጠይቁ።

ለተቀበሉት ሁሉ ግን፣ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው። ዮሐ 1፡12
---------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 25 ቀን ቀርቶታል

No comments:

Post a Comment