ዲቮሽን 315/07፥ ረቡዕ፥ ሐምሌ 15/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
አለማመናችንን እርዳ!!!!!!
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
አለማመናችንን እርዳ!!!!!!
አምናለሁ፣ አለማመኔን እርዳ። ማርቆስ 9፡ 24
የእምነት ነገር በጣም ከባድና ሐሳባዊ ሆኖባችሁ ያውቅ ይሆን? በተለይም በጣም በሚያስፈልጋችሁ ነገር ላይ፣ በጣም በጉጉት በምትጠብቁት ነገር ላይ፣ ጌታ በተደጋጋሚ እየተናገራችሁ ለእናንተ ግን ርቆባችሁ ይሆን? ጌታ ከተናገራችሁ ነገር በተቃራኒው በሕይወታችሁ እየሆነ ይሆን?
ሕይወታችሁን በቅድስና እየመራችሁ፣ ቃሉ እንደሚላችሁ እየተመላለሳችሁ፣ በሥፍራችሁ ሆናችሁ ሳለ፣ ነገሮች ግን እየተበላሹባችሁ ይሆን? እግዚአብሔርን ከመጠበቅ የተነሳም የመዛልና የስፍና ነገርስ ይሰማችሁ ይሆን? “ስለማታምኝ ነው/ ስለማታምን ነው እግዚአብሔር የተናገረሽን/ የተናገረህን ያልመለሰላችሁ” ተብላችሁስ በወገኖች ተመክራችሁ ይሆን?
እንግዲህ ነገሩ ካለማመናችን ከሆነ ለምን ተስማምተን አንጸልይም? እንዲህ በማለት፣ አብ አባት ሆይ፣ እኔ የማውቀው ማመኔን ነው፣ እኔ የማውቀው አንተን ተስፋ ማድረጌን ነው፣ ነፍሴ የምትመሰክርልኝ ኤልሻዳይነትህን ማመኔን ነው። ደግመህ ደጋግመህ በልዩ ልዩ መንገድ የተናገርኸኝ ነገር ያልሆነው ካለማመኔ ይሆንን? ወደጄ ሆይ፣ እባክህ አለማመኔን እርዳ። በድካሜ ላይ ተገለጥ፣ ጥርጣሬየን የመንፈስህ እሳት ይብላውና፣ ዛሬ በአዲስ እምነትና ኃይል ሙላኝ። ባለፈው ዘመኔ ሁሉ እንዳደረከው፣ እለምንሃለሁ፣ በወደድከው፣ ባከበርከው በልጅህ በኢየሱስ ስም እለምንሃለሁ፣ አለማመኔን እርዳ። ወደ ፈቃድህም አስገባኝ። ሰምተህኛልና ተባረክ።
--------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 51 ቀን ቀርቶታል፡፡
የእምነት ነገር በጣም ከባድና ሐሳባዊ ሆኖባችሁ ያውቅ ይሆን? በተለይም በጣም በሚያስፈልጋችሁ ነገር ላይ፣ በጣም በጉጉት በምትጠብቁት ነገር ላይ፣ ጌታ በተደጋጋሚ እየተናገራችሁ ለእናንተ ግን ርቆባችሁ ይሆን? ጌታ ከተናገራችሁ ነገር በተቃራኒው በሕይወታችሁ እየሆነ ይሆን?
ሕይወታችሁን በቅድስና እየመራችሁ፣ ቃሉ እንደሚላችሁ እየተመላለሳችሁ፣ በሥፍራችሁ ሆናችሁ ሳለ፣ ነገሮች ግን እየተበላሹባችሁ ይሆን? እግዚአብሔርን ከመጠበቅ የተነሳም የመዛልና የስፍና ነገርስ ይሰማችሁ ይሆን? “ስለማታምኝ ነው/ ስለማታምን ነው እግዚአብሔር የተናገረሽን/ የተናገረህን ያልመለሰላችሁ” ተብላችሁስ በወገኖች ተመክራችሁ ይሆን?
እንግዲህ ነገሩ ካለማመናችን ከሆነ ለምን ተስማምተን አንጸልይም? እንዲህ በማለት፣ አብ አባት ሆይ፣ እኔ የማውቀው ማመኔን ነው፣ እኔ የማውቀው አንተን ተስፋ ማድረጌን ነው፣ ነፍሴ የምትመሰክርልኝ ኤልሻዳይነትህን ማመኔን ነው። ደግመህ ደጋግመህ በልዩ ልዩ መንገድ የተናገርኸኝ ነገር ያልሆነው ካለማመኔ ይሆንን? ወደጄ ሆይ፣ እባክህ አለማመኔን እርዳ። በድካሜ ላይ ተገለጥ፣ ጥርጣሬየን የመንፈስህ እሳት ይብላውና፣ ዛሬ በአዲስ እምነትና ኃይል ሙላኝ። ባለፈው ዘመኔ ሁሉ እንዳደረከው፣ እለምንሃለሁ፣ በወደድከው፣ ባከበርከው በልጅህ በኢየሱስ ስም እለምንሃለሁ፣ አለማመኔን እርዳ። ወደ ፈቃድህም አስገባኝ። ሰምተህኛልና ተባረክ።
--------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 51 ቀን ቀርቶታል፡፡
No comments:
Post a Comment