ዲቮሽን 336/07፥ ረቡዕ፥ ነሐሴ 6/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
ምድረበዳየን ወደድኩት!!!!
ከሕዝብ ግርግር አወጣኸኝ፣ የሕዝቦች መሪ አድርገህ አስቀመጥኸኝ። መዝ 18፡43
በመከራ እያለፋችሁ ይሆን?
እግዚአብሔር ለእኛም ሆነ ለሰው ደስ የማይሉ የሕይወት መንገዶቻችንን እንዴት አድርጎ እንደሆነ ሳይታወቅ፣ ወደ መልካም ይለውጠዋል።
ድቅድቁን ጭለማ፣ ምንም ተስፋ የማይታይበት መንገዳችንን እግዚአብሔር ለሹመት ያደርገዋል።
ለካስ እኛ እያለቀስን፣ ለካስ እኛ እየከፋን የንግሥና ትምሕርት ቤት ገብተን ነው። ለዚያ እኮ ነው እግዚአብሔር ዝም የሚለው። ነገ የሚያደርግልልንን ስላየ፣ አይ ልጆቼ ያዘጋጀሁላችሁን ብታውቁ እኮ ያሁኑ ጨለማ እንደ ንጋት ፀሐይ ይሆንላችሁ ነበር እያለ፣ የእኛ ኢየሱስ ዝምምም ይላል።
ሰዎች ሲንቁን፣ ሲሰድቡን፣ ስንታመም፣ ስንሳቀቅ፣ ስንሸማቀቅ፣ የሚያጽናና ሲጠፋ፣ ሰው ፍለጋ ስንንከራተት ዓይናችን በእንባ ሲታጠብ---- ምስጢሩ እኮ፡ የንግስና ትምህርት ቤት ገብተን ነው።
እንዴ! እሱ እግዚአብሔር ነዋ! ሕይወታችን በመከራ እየተቀመመ ሙሉ ሰው ሊወጣን እኮ ነው።
እና ዛሬ "እግዚአብሔር ሆይ ምድረበዳየን እወደዋለሁ። ስለምድረበዳየ አመሰግንሃለሁ" ብንለውስ?
ግዴላችሁም፣ እንበል። አስደናቂ ነገር ከፊታችን ስላለ እኮ ነው! ገባችሁ ያልኩዋችሁ? በሁሉም አቅጣጫ ሙሉ ሆነን ልንገለጥ እኮ ነው! ባለሙሉ ስልጣን የክርስቶስ እንደራሴ ልንሆን ነው እኮ!!!
አባብላታለሁ፥ ወደ ምድረ በዳም አመጣታለሁ፥ ለልብዋም እናገራለሁ። ከዚያም የወይን ቦታዋን፥ የተስፋ በርም እንዲሆንላት የአኮርን ሸለቆ እሰጣታለሁ፤ በዚያም ከግብጽ ምድር እንደ ወጣችበት ቀን እንደ ሕፃንነትዋ ወራት ትዘምራለች። ሆሴዕ 2:16
---------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 30 ቀን ቀርቶታል
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 30 ቀን ቀርቶታል
No comments:
Post a Comment