ዲቮሽን 337/07፥ ሐሙስ፥ ነሐሴ 7/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
ኃያላን ወደቁ!!!!
ኃያላን እንዴት ወደቁ!? 2ኛ ሳሙ 1፤19
ስለጀግንነታቸው ምናልባት ሌሎች ሰዎች ከሚያውቋቸው በበለጠ፣ ሌሎች ወታደሮችና አብረዋቸው የሚኖሩ ሠራዊቶቻቸው ከሚያውቋቸው በላይ፣ ዳዊት ሳኦልንና ዮናታንን ይበልጥ ያውቃቸዋል። ሐያልነታቸው እስከምን እንደሆነ ከሌሎች እስራኤላውያን በተሻለ ዳዊት ልቅም እድርጎ ይገባዋል። እንዲያ ሲያርበደብዱት፣ በረሐ ለበረሐ ሲያስለቅሱት፣ ሲያስርቡት እና ሲያስጠሙት፣ ሲያንከራትቱት የነበሩትን እነዚህን ሁለት ሰዎች ዳዊት በደንብ አድርጎ የጀግነታቸውን ልክ ያውቀዋል።
ለካስ ሁሉም ልክ አለውና ጀግናም፣ ይወድቃል!!! ማመን ቢያቅተው ዳዊት እንዲህ አለ፤ ኃያላን እንዴት ወደቁ? 2ኛ ሳሙ 1፤19
እኛስ አሁን እያርበደበዱን፣ እያስደነገጡን፣ እያሳቀቁን ያሉ ስንት ጀግና የሆኑ፣ ሀጢያቶች፣ ልማዶች፣ ወጎች፣ እውቀቶች የሉም ብላችሁ ነው? መቼስ እንደ አቅም አቅማችን እኮ ብዙ ዓይነት ኃያላን፣ ሲያስጨንቁን እና ሲያሳድዱን አልኖሩም ብላችሁ ነው? አንዴ ኃጢአት ሲጀግንብን፣ አንዴ በሽታ ሲጀግንብን፣ አንዴ ሞት ሲጀግንብን፣ አንዴ ችግር ሲጀግንብን አልኖረም ብላችሁ ነው?
ግን ለኃያላንም የገዙበት ጊዜ በቃቸውና፣ ወደቁ። በቃ ወደቁ።።።።።።።። ምንም ማድረግ አይቻልም፡ ወ----ደ-----ቁ።።።።።። የኃያላን ሁሉ ኃያል ኢየሱስ መጣባቸዋ!!!
እግዚአብሔር የጽዮንን ምርኮ በመለሰ ጊዜ ሕልም እንጅ እውን አልመሰለንም ነበር። በዚያን ጊዜ አፋችን በሣቅ፣ አንደበታችንም በእልልታ ተሞላ። በዚያን ጊዜም በህዝቦች መካከል እግዚአብሔር ታላቅ ነገር አደረገላቸው ተባለ። እግዚአብሔር ታላቅ ነገር አደረገልን፤ እኛም ደስ አለን። መዝ 126: 1 አ---ሜ----ን።
---------ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 29 ቀን ቀርቶታል
No comments:
Post a Comment