ዲቮሽን 338/07፥ አርብ፥ ነሐሴ 8/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
አጎቴ ላባ ስሞኝ ተመለሰ!!!
በማግስቱም ላባ የልጅ ልጆቹን እንዲሁም ሴቶች ልጆቹን ስሞ መረቃቸው፤ ከዚያም ወደ አገሩ ተመለሰ። ዘፍ 31፡55
ያዕቆብ ለአጎቱ ለላባ በታማኝነት ሲገዛለት ኖረ። ላባም ሳያስበው አሪፍ ባሪያ አገኘ። “አንተማ የዐጥንቴ ፍላጭ የሥጋዬ ቁራጭ ነህ” እያለ፣ እያሞካሸው ለዓመታት ገዛው። ዘፍጥረት 13፡14
በኋላ በስተመጨረሻ ግን እግዚአብሔር በቃ ሲል፣ ያዕቆብ ኮበለለ። ለካስ ለገዥዎችም ገዥ አለ!!!!
ላባስ ከእንግዲህ ምን ስልጣን አለው!? ትንሽ ማንኮሻኮሽ መፍጠሩ ግን አልቀረም። አንዴ ሳትሰናበቱኝ ምነው? እያለ (አዛኝ ቅቤ አንጓች!!!!)፣ አንዴ አምላኮቼን ሰርቃችኋል እያለ (ጉድ ነው መቼም የሚሰረቅ አምላክ!!!!)፣ አንዴ ከፈለኩኝ ልጎዳህ እችላለሁ እያለ (አይሞክረውም ነበር፣ ድሮስ አዝኖለት ነው!!!!!) እንደ እብድ አስር ነገር ሲለፈልፍ ቆየና፣ ሀቁን አፈረጠው። "አምላካችሁ ያዕቆብን ደግም ክፉም እንዳትናገረው ብሎ አስጠነቀቀኝ" ብሎ እውነቱን ተናገረ!!!!! እሰይ የእኛ እግዚአብሄር!!!!
ከዚያም የልጅ ልጆቹን እንዲሁም ሴቶች ልጆቹን ስሞ መረቃቸው፤ ከዚያም ወደ አገሩ ተመለሰ። ዘፍ 31፡55።
ሲችል እያስፈራራ እያንገራገረ፣ ሳይችል እያባበለ፣ ሲገዛው የኖረውን ላባ፣ ያዕቆብ ለዘላለም ተገላገለው!!!!!!
ከዚያስ? ከዚያማ፣ ያዕቆብ ጉዞውን ቀጠለ። (32:1) እሰይ!!!!!!!!
ቁርስና ምሳ እየሰጡ ዘላለም ሊገዙን የወደዱ አጎቶቻችን ላባዎች ምንም ምርጫ ስለሌላቸው፣ ትእዛዝ ከሰማይ ስለወጣባቸው፣ ሲፈልጉ መርቀውን ሲፈልጉ ረግመውን ዛሬ ሔዱ። መሸሸጊያ ይሆኑናል፣ ያልናቸው አጎቶቻችን ላባዎች፣ መማጸኛ ይሆኑናል ብለን ሲገዙን የኖሩት ሁሉ፣ ዛሬ እየሳሙን ወደ አገራቸው ተመለሱ።
ዛሬ፣ ለዘመናት እንደ ላባ አጎት የሆኑባችሁ ሁሉ፣ ለዘላለም ሔደዋል።
አጎቴ ላባ ስሞኝ ተመለሰ!!! (Uncle Laba kissed me & departed from me FOREVER & returned to his place)
ያልኩት ገብቷችኋል? ከዚያስ?፣ ከዚያማ እንደ ያዕቆብ ጉዞአችንን ቀጠልና!!! ጉዞ እግዚአብሔር ወደ አየልን……..
ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሰራው። መክ 3:11
ማን?
ኢ-----የ-----ሱ-----ስ።
---------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 28 ቀን ቀርቶታል
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 28 ቀን ቀርቶታል
No comments:
Post a Comment