Saturday, August 15, 2015

ጨዋታችን ተቀየረ!!!!!

ዲቮሽን 339/07፥ ቅዳሜ፥ ነሐሴ 9/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
ጨዋታችን ተቀየረ!!!!!
ያዕቆብም ደግሞ ጉዞውን ቀጠለ፣ የእግዚአብሔርም መላእክት ተገናኙት። ዘፍ 32፡1
መቼም ሰውና ሰው ሲገናኝ እና ሰውና መልአክ ሲገናኝ ጨዋታው አንድ አይነት አይሆንም። ከአጎቴ ላባ ቤት እኮ ባዶ እጃችንን አልወጣንም፤ መሰለን እንጂ።
ብዙ ነገር በዝብዘን፣ ማርከን፣ ተትረፍርፈን ወጣን። አሁን ጠረናችን መላእክትን መሳብ ጀመረ። አሁን እንቅፋት የሚሆኑ ሰዎች ሳይሆኑ፣ አሁን መላእክትን በአካል ማየት ጀመርን። መዓዛችን ተቀየራ!!!!
አጎቴ ላባ ከመሔዱ አፍታም ሳይቆዩ የመላእክት መምጣት አይገርማችሁም!! በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ሁሉ ስላንተ ያዛቸዋልና። መዝ 91:11 This is entirely a divine design.
በመንገድ ስንሔድ አሳዳጅ አይደለም ያኘነው-መላእክትን ነው። ምን ምን አሏችሁ? ምን ምን አጫወቷችሁ? ምን ምስጢር ነገሯችሁ? ምን መልእክት አመጡላችሁ? ጉድ ነው መቼም! እንዴት ታድለናል! መላእክቱን ስለእኛ የሚያዝ እግዚአብሔር ይባረክ!!!!! አሜን!!!!!
አሁን እናት አይመክረን አባት፣ እህት አይመክረን ወንድም፣ አጎታችን ላባ አያስፈራራን፣ ያ ሊገድለን ቀን ቀጠሮ ይዞ የነበረው ወንድማችን ዔሳው ጦር አይሰብቅብን። መላእክትን አግኝተናላ!!!!
እራሳቸው መላእክት ተልከው መጡልን---- በአካል አየናቸው!!!! ታድለን!!!! እፎይ!!!!!!!
በቃ ተለወጥን! እንዴት ግሩም ነገር ነው! ገና ከእናታችን ማህፀን ሳንወጣ እኮ ነው ትንቢት የተጀመረው። ጉዞ ወደ ቃልኪዳናችን........... ደስ ሲል!
ታዲያ እንዳትዘናጉ፣ ከአጎቴ ላባ ጋር ተሳስመን እንደተለያየነው ሁሉ ከወንድሜ ዔሳው ጋርም እንዲሁ አድርጉ። እሽ??? አደራችሁን፣ ምንም መዳበል የሚባል ኑሮ የለም!!!!!!
እዛው በሩቁ፣ እሽ??? አደራ!!! አጎቴ ላባ ወደ አገሩ እንደተመለሰው ሁሉ፣ ወንድሜ ዔሳውም ወደ አገሩ በሰላም ይመለስ። ደባል አንፈልግም!!!! እንደገና ጭቅጭቅ ውስጥማ አንገባም!!!! ስንት ስራ የሚጠብቀን ሰዎች እኮ ነን!
ከዚያም ዲያብሎስ ትቶት ሄደ፣ መላእክትም አገለገሉት። ማቴ 3:11
---------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 27 ቀን ቀርቶታል

No comments:

Post a Comment