ዲቮሽን 321/07፥ ማክሰኞ፥ ሐምሌ 21/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
አትምረጡ!!!!!
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
አትምረጡ!!!!!
የምታመልኩትን ዛሬ ምረጡ። እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን። ኢያሱ 24፡ 15
ኢያሱ የእሥራኤላውያን ነገር አንዴ ያዝ አንዴ ለቀቅ ያለ ዘይቤ ቢይዝበት ደከመውና፣ ምክሩን ሁሉ ሲፈልጉ ሲቀበሉ፣ ሳይፈልጉ ሲጥሉ፣ ሞቅ ያላቸው እንደሆነ ጣዓት ሲያመልኩ፣ መከራ ሲደርስባቸው ወደ እግዚአብሔር ሲመለሱ፣ እንዲያው ታከተውና፣ ራሴን ባድንስ፣ ሲፈልጉ እግዚአብሔርን ያምልኩ፣ ካለፈለጉ ይተውት በማለት ይመስለኛል፣ “የምታመልኩትን ዛሬ ምረጡ። እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን።” ኢያሱ 24፡ 15 በማለት እግዚአብሔርን የማምለክን ጉዳይ ምርጫ ውስጥ ያስገባላቸው።
ዛሬ ግን እኔ እንዲህ እላችኋለሁ! ግዴላችሁም አትምረጡ!!! በሞትና በሕይወት መካከል ሰፊ ልዩነት አለና ለማን ይድላው ብላችሁ ነው፣ ሞትን የምትመርጡት? በሲኦልና በመንግስተ ሰማያት መካከል ከቃላት በላይ የሆነ ልዩነት አለና፣ ለማን ይመቸው ብላችሁ ነው ሲኦልን የምትመርጡት?
ዘመኑ የምርጫ ነው። ሰፊ አማራጭ አለን። ብንፈልግ ኢየሱስን እንደ ሞራል አስተማሪ ልንቀበለው እንችላለን፣ ብንፈልግ እንደ አሪፍ መሪ ልንቀበለው እንችላለን፣ እንደ ትልቅ ምሁርም ልናየው እንችላለን፣ በየወቅቱ ከተነሱት ፈላስፎችም እንደ አንዱ ማየትም መብታችን ነው። ግን ይህ ሁሉ ከሞት አያድነንም። ከሞት የሚያድነው፣ ኢየሱስን እንደ እግዚአብሔር ልጅ መቀበል ብቻ ነው።
ስለዚህ ግዴላችሁም፣ ኢየሱስን ከስነልቦና ምሁራን ጋር አታወዳድሩት፣ ከፈላስፎችም ጋር አታነጻጽሩት። እንዲህ ያለው እውቀታችን የትም አያደርሰንም፣ ከዘላለም ሞት በቀርም የሚያመጣልን ምንም ነገር የለም። ለዚህም ነው ጳውሎስ፣ “በውሸት እውቀት ከተባለ ለዓለም ከሚመች ከከንቱ መለፍለፍና መከራከር እየራቅህ የተሰጠህን አደራ ጠብቅ፣ ይህ እውቀት አለን ብለው አንዳንዶች ስለእምነት ስተዋልና ያለው።” 2 ጢሞ 6፡20።
ኢየሱስ ያድናል!!!!!
አባትዬ፣ እንዲህ እንድናገር ድፍረቱንም ዓቅሙንም ስሰጠህኝ አመሰግንሃለሁ። የምድረበዳየ ኢየሱስ ሆይ፣ እወድሃለሁ። ወንዶች እና ሴቶች ልጆችህ ሁሉ አንተን በማወቅ እንዲሞሉ አሁን መንፈስህን አፍስስባቸው። ሰምተህኛልና ተባረክኝ።
--------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 45 ቀን ቀርቶታል
ኢያሱ የእሥራኤላውያን ነገር አንዴ ያዝ አንዴ ለቀቅ ያለ ዘይቤ ቢይዝበት ደከመውና፣ ምክሩን ሁሉ ሲፈልጉ ሲቀበሉ፣ ሳይፈልጉ ሲጥሉ፣ ሞቅ ያላቸው እንደሆነ ጣዓት ሲያመልኩ፣ መከራ ሲደርስባቸው ወደ እግዚአብሔር ሲመለሱ፣ እንዲያው ታከተውና፣ ራሴን ባድንስ፣ ሲፈልጉ እግዚአብሔርን ያምልኩ፣ ካለፈለጉ ይተውት በማለት ይመስለኛል፣ “የምታመልኩትን ዛሬ ምረጡ። እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን።” ኢያሱ 24፡ 15 በማለት እግዚአብሔርን የማምለክን ጉዳይ ምርጫ ውስጥ ያስገባላቸው።
ዛሬ ግን እኔ እንዲህ እላችኋለሁ! ግዴላችሁም አትምረጡ!!! በሞትና በሕይወት መካከል ሰፊ ልዩነት አለና ለማን ይድላው ብላችሁ ነው፣ ሞትን የምትመርጡት? በሲኦልና በመንግስተ ሰማያት መካከል ከቃላት በላይ የሆነ ልዩነት አለና፣ ለማን ይመቸው ብላችሁ ነው ሲኦልን የምትመርጡት?
ዘመኑ የምርጫ ነው። ሰፊ አማራጭ አለን። ብንፈልግ ኢየሱስን እንደ ሞራል አስተማሪ ልንቀበለው እንችላለን፣ ብንፈልግ እንደ አሪፍ መሪ ልንቀበለው እንችላለን፣ እንደ ትልቅ ምሁርም ልናየው እንችላለን፣ በየወቅቱ ከተነሱት ፈላስፎችም እንደ አንዱ ማየትም መብታችን ነው። ግን ይህ ሁሉ ከሞት አያድነንም። ከሞት የሚያድነው፣ ኢየሱስን እንደ እግዚአብሔር ልጅ መቀበል ብቻ ነው።
ስለዚህ ግዴላችሁም፣ ኢየሱስን ከስነልቦና ምሁራን ጋር አታወዳድሩት፣ ከፈላስፎችም ጋር አታነጻጽሩት። እንዲህ ያለው እውቀታችን የትም አያደርሰንም፣ ከዘላለም ሞት በቀርም የሚያመጣልን ምንም ነገር የለም። ለዚህም ነው ጳውሎስ፣ “በውሸት እውቀት ከተባለ ለዓለም ከሚመች ከከንቱ መለፍለፍና መከራከር እየራቅህ የተሰጠህን አደራ ጠብቅ፣ ይህ እውቀት አለን ብለው አንዳንዶች ስለእምነት ስተዋልና ያለው።” 2 ጢሞ 6፡20።
ኢየሱስ ያድናል!!!!!
አባትዬ፣ እንዲህ እንድናገር ድፍረቱንም ዓቅሙንም ስሰጠህኝ አመሰግንሃለሁ። የምድረበዳየ ኢየሱስ ሆይ፣ እወድሃለሁ። ወንዶች እና ሴቶች ልጆችህ ሁሉ አንተን በማወቅ እንዲሞሉ አሁን መንፈስህን አፍስስባቸው። ሰምተህኛልና ተባረክኝ።
--------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 45 ቀን ቀርቶታል
No comments:
Post a Comment