ዲቮሽን 317/07፥ አርብ፥ ሐምሌ 17/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
ካላየሁ አላምንም!!!!!
የችንካሩን ምልክት በእጆቹ ካላየሁ..... እጄንም በጎኑ ካላገባሁ አላምንም አላቸው። ዮሐንስ 20፡ 25
እንግዲህ ክርስትና የመጠማት፣ የመፈለግ፣ እና ከኢየሱስ ጋር የሚኖረን የግል ልምምድ ነው። አንዱ ጋር የሚኖር ልምምድ ሌላው ዘንድ ላይኖር ይችላል። ኢየሱስ የግል አዳኛችን ነው። በግላችን እሱን እንፈልጋለን፣ በደረስንበት እንመላለሳለን። መቼም እመን/ እመኚ ስለተባልን ማመን አንችልም። መሆን የምንችለው ራሳችንን ነው።
ስለዚህ ዛሬ በጌታ ፊት በፍጹም ቅንነትና እውነተኛነት ብንቀርበስ? ቶማስ ያደረገው እንደዚህ ነው። ተጠራጣሪ ልብ እያለው ራሱን አማኝ አስመስሎ በጌታ ፊት አልተመጻደቀም፤ በወንድሞቹም መካከል አልዋሸም። ይልቅስ በይፋ በግልጽ “የችንካሩን ምልክት በእጆቹ ካላየሁ፣ ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ካላስገባሁ፣ እጄንም በጎኑ ካላገባሁ አላምንም አላቸው። ዮሐንስ 20፡ 25። የልቡን ቅንነት ያየው ኢየሱስም አላሰፈረውም። የቶማስንም የልብ ጭንቅ እና ጥርጣሬ መፍትሔ አበጀለት።
እንግዲህ ምናልባት እንዲህ ያለ ሁኔታ ውስጥ ካላችሁ ለምን ተስማምተን አንጸልይም፣ ኢየሱስ ሆይ ከስጋ ድካማችን የተነሳ፣ ከዘገየ ተስፋችንም የተነሳ፣ በጥርጣሬ ውስጥ ላለን ሁሉ እባክህ ዛሬ ተገለጥ። እባክህ ወዳጄ ሆይ፣ እኛም በዓይኖቻችን እንይህ፣ በእጆቻችንም እንዳስህ፣ እንደ ቶማስም ጌታየ አምላኬ እንበልህ። ዘመዴ ሆይ ተባረክ።
--------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 49 ቀን ቀርቶታል፡፡
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 49 ቀን ቀርቶታል፡፡
No comments:
Post a Comment