ዲቮሽን 349/07፥ ማክሰኞ፥ ነሐሴ 18/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
በምድረበዳችን አፈራን!!!!!!
እግዚአብሔር በመከራዬ አገር አፈራኝ። ዘፍ 41፡52
እንግዲህ እግዚአብሔር የኃይሉ ልክ ከሰው ዓእምሮ በላይ መሆኑን ሊያሳየን ተንቀሳቅሷል። እኛ አንዳንዴ እግዚአብሔርን ለሰው እንዳደረገው እንዲያደርግ ስለምንፈልግ የምንጠብቀውም ያንኑ ነው። እሱ ግን ምንም እንኳን ዓላማው አንድ ቢሆንም፣ እሱም እኛን ማዳን ሲሆን፤ አሰራሩ በራሱ ምርጫ ላይ ላይ የተመሠረተ ነው።
መከራችንን እግዚአብሔር አስረስቶ ዝም አላለም። አያልቅበት የእኛ ጌታ! ደግሞ አበዛን። ፍሬ አፈራን። ጠላታችን ሊገለን፣ሊያሳብደን፣ እስረኞችና ባሪያዎች አድርጎ ሊያስቀረን ነበር ወደ ምድረ በዳ የወሰደን። ከሰው ከዘመድ ነጥሎ፣ ከአማኞች ከወገናችን ሁሉ ነጣጥሎ፣ ጓደኞቻችንን ሁሉ ከእኛ አርቆ፣ አንድ ቀን በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ገብተን ራሳችንን እንድንጠላ ከዚያም ራሳችንን እንድናጠፋ ነበር ዓላማው። በዘላለም ፍቅር እንደተወደድን ያላወቀ ጅል!!!!!!
እኛ እኮ በዘላለም ፍቅር ተ-ወ-ደ-ና-ል። ገና ሳንወልድ፣ ገና ሳንጸነስ፣ ፍሬያማ እንድንሆን ተጠርተናል። ስለዚህ ኢየሱስ ሁሉንም ለበጎ አደረገልን። አሁንስ ጠፍተው ይሆናል እያሉ ሰዎች ሁሉ ሲጠብቁን ጭራሽ ተገኘን፣ ደርቀው ቀርተዋል እያሉ ሲያሟርቱብን እኛ ግን ለምልመን አረፍነው። አይገርምም ወገኖቼ?
በምድረበዳ ላይ ማፍራት የሚቻለው ከኢየሱስ ደም የተነሳ ብቻ ነው። እና በመከራችን አገር አፈራን። ኤፍሬም ሆነልን። እንግዲህ ክብር ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ እንሰጣለን እንጅ ሌላ ምን እንላለን!!!! አንድ ነጠላ ነበርን፣ ግን አልፈን ተርፈን አገር ሆንን! ዳርቻችን ሰፋ!
ሕዝብን አበዛህ፣ አቤቱ ሕዝብን አበዛህ፣ አንተም ተከበርህ፣ የአገሪቱንም ዳርቻ ሁሉ አሰፋህ። ኢሳ 26፡15
---------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 17 ቀን ቀርቶታል
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 17 ቀን ቀርቶታል
No comments:
Post a Comment