ዲቮሽን 348/07፥ ሰኞ፥ ነሐሴ 18/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
ምናሴ ሆነልን!!!!!!
እግዚአብሔር መከራዬንና የአባቴን ቤት አስረሳኝ። ዘፍ 41፡50
ያ ሁሉ ለቅሶ ያ ሁሉ የማይታለፍ የሚመስለው የመከራ መንገዳችን አለፈ። በየመንገዱ በየአደባባዩ ስናለቅስ በየቤተክርስትያኑ ስናለቅስ፣ በየጓደኞቻችን ስናለቅስ፣ የጌታ የማዳን ክንድ ወዴት ነው እያልን እንባችን እንደ ጎርፍ ሲፈስ .... በቃ ጌታ በቃ ሲለው ሃዘናችን አበቃ። ረሳነው። እግዚአብሔር አስረሳን።
የሚያድነን እና የሚታደገን ማነው? ወዴት ቤተክርስትያንስ ይኬዳል? እውነት የእግዚአብሔር ቃል ይሠራል ወይ እያልን የተንከራተትንበት ያ ጊዜ አለፈ። አሁን እኮ አንዳንዶቻችን የመከራችንን ዓይነት እንኳን በቅጡ አናስታውሰውም። ምናሴ ሆነልን።
አሁን ዮሴፍ ወንድሞቹ ሊገድሉት ሲማከሩ፣ ከዚያም ሲሸጡት፣ ከዚያም የጲጥፋራ አሽከር ሲሆን፣ ከዚያም ሲሾም፣ ከዚያም እሥር ቤት ሲወርድ፣ በእስር ቤት ላገኘው የመጠጥ አሳላፊ፣ ከዚህ እስር ቤት አስወጣኝ እያለ ሲማጸን፣ ሰውዬውም ሲረሳው፣ ...... አ..ቤ....ት... ስንት የጨለማ ጊዜ እኮ አለፈ!!!
እውነት በዚያን ጊዜ ዮሴፍ ስለራሱ ምን ይሰማው ይሆን? ያው ጠዋትና ማታ በሰው አገር ታሥሮ እንባውን ቁርስ ምሳና እራት አድርጎ፣ በትካዜ በጨለማ ቤት ሲቀመጥ... በግብጽ ምድር ላይ ኃላፊ፣ የንጉሥ አማች፣ የትውልዱ ተስፋ ይሆናል ብሎ ማን አመነ!!! ግን ይገርማል! ሆነ። በቃ ሆነ። ምክንያቱም መከራው የበዛበት እኮ ባለ ራእይ ስለነበረ ነው።
እና ዛሬ ምናሴ ሆነልን። መከራችንን እግዚአብሔር አስረሳን። ታዲያ ደስ አይልም-ወገኖቼ!!!!
የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፣ እግዚአብሔር ግን ከሁሉ ያድናቸዋል። መዝ 34፡19
---------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 18 ቀን ቀርቶታል
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 18 ቀን ቀርቶታል
No comments:
Post a Comment