Wednesday, August 26, 2015

መሠቃየታችን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር!!!!!

ዲቮሽን 350/07፥ ረቡዕ፥ ነሐሴ 20/07 ዓ/ም 
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
መሠቃየታችን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር!!!!!
መድቀቁና መሰቃየቱ ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር። ኢሳ 53፡ 10
እና ዛሬ ልላችሁ የምፈልገው፣ በመከራ መድቀቃችን እና መሰቃየታችን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር ነው ልላችሁ የምወደው። በእርግጥ መከራን ያየ ሰው ምን ማለቴ እንደሆነ ያውቀዋል።
ስንንከራተት፣ ስንዋረድ፣ የሰው መሳቂያ እና መሳለቂያ ስንሆን፣ እኛም በሰቀቀን ሰውነታችን ሲያልቅ፣ አሄሄሄ! ስንቱን ልንገራችሁ.... አንድ አይዞህ ባይ ሲጠፋ፣ ሰውም እሰይ ክፋቱ አገኘው! እያለ አፉን ሲከፍትብን! ለምን መሰላችሁ? ብዙ ድል፣ ብዙ ምስጋና፣ ብዙ ዝማሬ ወደፊት ይጠብቀን ስለነበረ ነው።
እኛ ተራ ሰዎች ስላላይደለን፣ የሚገጥመን መከራም ተራ አይደለም። እግዚአብሔር ማንን እንደጣለ ይጥለናል? እስኪ እግዚአብሔርን የሚከስ ማነው? የት ላይ በቃሉ ሳይገኝ ቀረ! ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፣ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይካፈላል። ኢሳ 53፡12 እንደተባለ፣ ውሎአችን ከኃያላን እና ከነገስታት ጋር ስለሆነ፣ የተጠራነውም ለዓለም ሁሉ ስለሆነ፣ ገና የብዙዎች መጠለያም ስለምንሆን እኮ ነው ድቅቅ ስቅይት ያልነው።
እንጅ ለሞትማ ቢሆን፣ ብዙዎች እኮ ሞተዋል!!! እኛም እንደ መድቀቃችን እና መሰቃየታችን ቢሆን ኖሮማ ድራሻችንም አይገኝ ነበር እኮ! ግን ይህን ያየነውን የዳሰስነውን፣ የቀመስነውን፣ የበላነውን ኢየሱስን ለዓለም ሁሉ ማዳረስ ስላለብን ነው ያ ሁሉ መከራ በእኛ ላይ የሆነው። እና ለዛሬዋ ቀን ሲል ነው እንዲህ መድቀቃችን እና መሰቃየታችን!!!!!!!
እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤ በእርስዋ ሐሤትን እናድርግ ደስም ይበለን። መዝ 118፡24
---------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 16 ቀን ቀርቶታል

No comments:

Post a Comment