ዲቮሽን 333/07፥ እሁድ፥ ነሐሴ 3/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
"ነበር” አያድንም!!!!!!
በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበር። ማቴ፡ 27፡ 54
ከምሬ ነው የምላችሁ፣ አዳኙን ኢየሱስን አለመቀበል ምንኛ ከንቱነት ነው? ምንኛስ አለመታደል ነው? ከዘላለም ሕይወትስ የዘላለም ሞትን መምረጥ ምንኛ አሳዛኝ ነገር ነው? ምንስ አይነትስ ድንዛዜ ነው? ምንስ አይነትስ ፍርጃ ነው? የሐዋርያት ሥራ፡ 1፡11 “ልክ ወደ ሰማይ ሲወጣ እንዳያችሁት በዚሁ ሁኔታ ይመለሳል”፣ እንደተባሉት እንደዋዘኞቹ እንደ ገሊላ ሰዎች መሆንስ ምንኛ ዘግናኝ ነገር ነው? ኧረ ለወሬም አይመች!!!!!
በሞላ ጎደለ ስሌት ኢየሱስን አለመቀበል ምንኛ አስፈሪ ነው? ዛሬ፣ ቀኑ ዛሬ ተብሎ ሲጠራ እባካችሁ መመለስ ይሁንልን? እባካችሁ ኢየሱስ አይለመድም። እባካችሁ ሁሉም ነገር ቀሪ ነው።
ብዙ ስራዎችም ቢኖሩን፣ ወይም ደግሞ ራእዪያችንን ለማሳካት ደፋ ቀና ስንል ብንውልም፣ እባካችሁ ሞት የሚባል ጉዳይ ይጠብቀናል እኮ!!!!! የሙታን ትንሳዔም በእርግጥ አለ።
ኢየሱስም ሲመጣ ለፍርድ እንጅ ዳግመኛ ሊሰቀልልን እንዳልሆነ ለነፍሳችሁ ንገሯት። ያለመታከትም ለሰዎች ንገሩ! እኛም ቀድመን ከሰማነው ወንጌል ሌላ አዲስና ልዩ ወንጌል አንስማ፣ አንቀበል። በሲኦል ውስጥ ሆኖ፣ “በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበር”። ማቴ፡ 27፡ 54 ማለት እኮ ከሞት አያስመልጥም።
ያን ጊዜማ ወደን ሳይሆን ተገደን ማለታችን የት ይቀራል???
እኔ ግን የሚቤዠኝ ሕያው እንደሆነ፣ በመጨረሻም ዘመን በምድር ላይ እንዲቆም፣ ይህ ቁርበቴም ከጠፋ በሁዋላ በዚያን ጊዜ ከሥጋየ ተለይቼ እግዚአብሔርን እንዳይ አውቃለሁ። ኢዮብ 19:26
እነሆ የመዳን ቀን ዛሬ ነው!!!!!!!!!
---------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 33 ቀን ቀርቶታል
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 33 ቀን ቀርቶታል
No comments:
Post a Comment