ዲቮሽን 334/07፥ ሰኞ፥ ነሐሴ 4/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
አትገረም!!!!!!!!
ዳግመኛ መወለድ አለባችሁ ስላልሁህ አትገረም። ዮሐ 3፡7
ሰዎች ከከባድ አደጋ ሲተርፉ፣ ወይም ከጦርነት ልጆቻቸው ተርፈው ሲመለሱ፣ ከአስደንጋጭ ሁኔታዎች ሲያመልጡ ወ.ዘ.ተ ..... “ዛሬ ዳግም እንደ ተወለድኩ እቆጥረዋለሁ” ይላሉ።
መቼም ብዙው ሰው እኮ፣ ዳግም በምድር ላይ እንደ ህጻን የመኖር እድል ቢሰጠው፣ የኖረው ህይወቱን መድገም የሚፈልግ ሰው ኢምንት ነው። አብዛኞቻን ብዙ ስህተቶቻንን አስተካክለን፣ መኖር ነው የምፈልገው። ከህይወት ምእራፎቻችን ልናስታውሳቸው የማንፈልጋቸው ክፍሎች ስላሉን፣ ያንን እያጠፋን መልካሙን ብቻ እያዳበረን መቀጠል እንፈልጋለን።
ታዲያ ሰዎች ዳግም እንደማይወለዱ እያወቁ፣ ለምን “ዛሬ ዳግም እንደ ተወለድኩ እቆጥረዋለሁ” ይላሉ?
መልሱ ምንም ሰምና ወርቅ የለውም፣ ምንም ዓይነት ቅኔም የለውም። ነፍሳቸው የዳግም መወለድን ጥቅም ስለምታወቀው ያንን እየመሰከረችላቸው ነው።
ምናልባት ዛሬስ በቤተክርስትያናችን ውስጥ፣ ዳግም ያልተወለድን ሰዎች እንኖር ይሆን? ኢየሱስስ ለኒቆዲሞስ፣ “ዳግመኛ መወለድ አለባችሁ ስላልሁህ አትገረም” የሚለው ምን ማለት ፈልጎ ነው?
መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን። ኤፌ 2:10
---------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 32 ቀን ቀርቶታል
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 32 ቀን ቀርቶታል
No comments:
Post a Comment