ዲቮሽን 330 / 07 ሓሙስ ሓምሌ 30/07
( ወንድም ጌታሁን ሓለፎም )
“ ሕይወት ግልጽ ናት ”
( ወንድም ጌታሁን ሓለፎም )
“ ሕይወት ግልጽ ናት ”
“ ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን ፤ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውንም የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን ” 1ኛ ዮሓ 1፡-2
እርግጥ ነው ! እውነተኛውን የመለኮት ፍቅር የቀመሰና ያጣጣመ ፤ የጌታን ቸርነት እና እርህራሔ ያየና የተረዳ ፤ ህያው የሆነውን ሰማያዊ ድምጹን የሰማ ፤ በአምሳሉ የተፈጠረ የስው ልጅ ይቅር እና ጉእዛን ብለን የምንጠራቸው ተራሮች እና ወንዞች እንኳን ሳይቀሩ ስለ እግዚአብሔር አምላክነት ያወራሉ ፤ ስለ ጌትነቱ ይዘምራሉ ስለ ሁሉን ቻይነቱ እልል ይላሉ ። ያውቁታልና !
በአብ ዘንድ ለዘመናት ተሰውሮ የበበረው የዘላለም ሕይወት በመሲሁ በኩል ለሰው ልጆች ዘላለማዊ ደህንነት ተገልጧልና እየተደነቅን እየተገረምን የማዳኑን የምስራች እንናገራለን ፤ አዎ የምስራቹ ይዘመራል ፤ ይሰበካል ፤ እንደ እብድ ይጮሓል ቃላችንም ምድሪቷን ይከድናል ! ዝም ማለት አይቻለንም !
ይሔ የተገለጠው ሕይወት ዘላለማዊ የሆነ በረከት ነውና በመካከላችንም የከበረ ስለሆነ ይህንን ስለ አየን እና ስለቀመስን እንዲሁም ስለዳሰስነው እናወራላችኃለን ያየነውን እና የቀመስነውን በውነት እንናገራለን እንጽፍላችኋለን !
ስንከተለው ላፍታም አልተለየንም እና ታማኝነቱን አረጋግጠናል ! ስናዝን አጽናንቶናል ፤ ተስፋ ስንቆርጥ ወደ ነፍሳችን ተጠግቶ አይዟችሁ ብሎናል ስለዚህም እኛ ፍቅሩን የቀመስን ፤ አደራረግ እና አሰራሩን ያየን ፤ ምስክርነታችን እውነት ነውና እንጽፍላችሗለን ።
እነ ሓዋርያው ዮሓንስ በነበያት የትንቢት ቃል ስለ ሰው ልጆች ኃጢያት ሊሞት እና በሦስተኛው ቀን ሊነሳ ይገባዋል ስለ ተባለለት አዳኝ “ኢየሱስ ክርስቶስ ” በምድር ላይ ሦስት አመት ተኩል ባገለገለበት ወቅቶች አብረውት እየወጡ እየገቡ በቅርብ ሥራውን አይተዋልና ቀርበውም ዳሰውታልና ፤ መልካምነቱን ታእምራቱን ጠግበዋል እና ዝም ሊሉ አልቻሉም ነበር !
እኛም መሲሁን አግኝተነዋልና ደግሞም ስለቀመስነውና ስለዳሰስነው እንናገራለን ። የሞተና ተስፋ የተቆረተበት ነገራችን በጌታ ትንሳኤ አግኝቶ እንደገና ህይወት ዘርቷልና ይህንን ሊያደርግ የሚቻለው ብቸኛው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው እያልን እናወራላችኋለን እንጽፍላችኋለን !
ክርስትና ሓይማኖት አይደለም ። ክርስትና እውነት እና ሕይይወት ነው ስለዚህ ይኖርበታል ፤ እንዲሁም የሚቀመስ ፤ የሚዳሰስ ደግሞም የሚታይ ነው እና ያጣጥሙታል ! ስለዚህም ያወሩታል ፤ ይዘምሩታል ይመሰክሩለታል ይጽፉታል ።
አሜን ! የክርስቶስ ወንጌል የተቸገሩትን ነጻ ለማውጣት ፤ የታሰሩትን ለመፍታት የታመሙትን ለመፈወስ እንዲሁም በአጋንንት የተያዙትን ነጻ ለመልቀቅ ወሳኝ ነውና የጌታን ማዳን በቀመሱና እውነትን በተረዱ የመንግስቱ ወራሾች ይሰበካል ፤ ይነገራል !
ሁላችንንም ካህናት እና የመንግስቱ ወራሾች ያደረገን መድሓኒአለም ይባረክ !
--------
እለታዊ ዲቮሽኑ ሊጠናቀቅ 36 ቀን ቀረው
እርግጥ ነው ! እውነተኛውን የመለኮት ፍቅር የቀመሰና ያጣጣመ ፤ የጌታን ቸርነት እና እርህራሔ ያየና የተረዳ ፤ ህያው የሆነውን ሰማያዊ ድምጹን የሰማ ፤ በአምሳሉ የተፈጠረ የስው ልጅ ይቅር እና ጉእዛን ብለን የምንጠራቸው ተራሮች እና ወንዞች እንኳን ሳይቀሩ ስለ እግዚአብሔር አምላክነት ያወራሉ ፤ ስለ ጌትነቱ ይዘምራሉ ስለ ሁሉን ቻይነቱ እልል ይላሉ ። ያውቁታልና !
በአብ ዘንድ ለዘመናት ተሰውሮ የበበረው የዘላለም ሕይወት በመሲሁ በኩል ለሰው ልጆች ዘላለማዊ ደህንነት ተገልጧልና እየተደነቅን እየተገረምን የማዳኑን የምስራች እንናገራለን ፤ አዎ የምስራቹ ይዘመራል ፤ ይሰበካል ፤ እንደ እብድ ይጮሓል ቃላችንም ምድሪቷን ይከድናል ! ዝም ማለት አይቻለንም !
ይሔ የተገለጠው ሕይወት ዘላለማዊ የሆነ በረከት ነውና በመካከላችንም የከበረ ስለሆነ ይህንን ስለ አየን እና ስለቀመስን እንዲሁም ስለዳሰስነው እናወራላችኃለን ያየነውን እና የቀመስነውን በውነት እንናገራለን እንጽፍላችኋለን !
ስንከተለው ላፍታም አልተለየንም እና ታማኝነቱን አረጋግጠናል ! ስናዝን አጽናንቶናል ፤ ተስፋ ስንቆርጥ ወደ ነፍሳችን ተጠግቶ አይዟችሁ ብሎናል ስለዚህም እኛ ፍቅሩን የቀመስን ፤ አደራረግ እና አሰራሩን ያየን ፤ ምስክርነታችን እውነት ነውና እንጽፍላችሗለን ።
እነ ሓዋርያው ዮሓንስ በነበያት የትንቢት ቃል ስለ ሰው ልጆች ኃጢያት ሊሞት እና በሦስተኛው ቀን ሊነሳ ይገባዋል ስለ ተባለለት አዳኝ “ኢየሱስ ክርስቶስ ” በምድር ላይ ሦስት አመት ተኩል ባገለገለበት ወቅቶች አብረውት እየወጡ እየገቡ በቅርብ ሥራውን አይተዋልና ቀርበውም ዳሰውታልና ፤ መልካምነቱን ታእምራቱን ጠግበዋል እና ዝም ሊሉ አልቻሉም ነበር !
እኛም መሲሁን አግኝተነዋልና ደግሞም ስለቀመስነውና ስለዳሰስነው እንናገራለን ። የሞተና ተስፋ የተቆረተበት ነገራችን በጌታ ትንሳኤ አግኝቶ እንደገና ህይወት ዘርቷልና ይህንን ሊያደርግ የሚቻለው ብቸኛው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው እያልን እናወራላችኋለን እንጽፍላችኋለን !
ክርስትና ሓይማኖት አይደለም ። ክርስትና እውነት እና ሕይይወት ነው ስለዚህ ይኖርበታል ፤ እንዲሁም የሚቀመስ ፤ የሚዳሰስ ደግሞም የሚታይ ነው እና ያጣጥሙታል ! ስለዚህም ያወሩታል ፤ ይዘምሩታል ይመሰክሩለታል ይጽፉታል ።
አሜን ! የክርስቶስ ወንጌል የተቸገሩትን ነጻ ለማውጣት ፤ የታሰሩትን ለመፍታት የታመሙትን ለመፈወስ እንዲሁም በአጋንንት የተያዙትን ነጻ ለመልቀቅ ወሳኝ ነውና የጌታን ማዳን በቀመሱና እውነትን በተረዱ የመንግስቱ ወራሾች ይሰበካል ፤ ይነገራል !
ሁላችንንም ካህናት እና የመንግስቱ ወራሾች ያደረገን መድሓኒአለም ይባረክ !
--------
እለታዊ ዲቮሽኑ ሊጠናቀቅ 36 ቀን ቀረው
No comments:
Post a Comment