ዲቮሽን 329/07፥ አርብ፥ ነሐሴ 1/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
ተስፋዎቻችን!!!
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
ተስፋዎቻችን!!!
አንተ ለምድር ዳርቻ ሁሉ፣ በርቀት ላለውም ባሕር ተስፋ ነህ። መዝ 65:5
መቼም ይህ ድብልቅልቁ የወጣበት ዘመን፣ ከእግዚአብሔር ይልቅ ብዙ ሌሎች 'ተስፋዎቻችንንና እና ረዳቶቻችንን' እያስቆጠረን ነው። በአይነትም በብዛትም እጅግ በርካታ ስለሆኑ እነሱን ሁሉ እዚህ መጥቀስ አይቻልም። እኔም እናንተም እናውቃቸዋለን እኮ!!!! ለቁጥር የሚያዳግቱ 'ረዳቶቻችን እና ተስፋዎቻችን' በዙሪያችን አሉ።
እንዲያው እነዚህ የተደገፍናቸው ነገሮች ሸንበቆ ሲሆኑብን፣ “የሚረዳኝ የለምና ከእኔ አትራቅ፣ አሁንስ ተስፋዬ ማነው? እግዚአብሔር አይደለምን?፣ ወይም በሰው ከመደገፍ በእግዚአብሔር መደገፍ ይሻላል፣ ወ.ዘ.ተ. የሚሉ እንጉርጉሮ አዘል ጥቅሶችን ለይምሰል ያህል እንጠቀማለን።
ግን ሕይወታችን እኮ የሚቀናበረው እግዚአብሔር እንዳለው ነው እንጅ፣ በደገፋዎቻችንን ብዛት እንዳልሆነ የየግል ሕይወታችን ምስክር ነው። ስንቱ የተደገፍንበት መንገድ ላይ እየቀረ እኮ ባላስልጣኑ ኢየሱስ ብቻ ዛሬም ነገም ለዘላለምም ከእኛ ጋር ይዘልቃል።
ስለዚህ፣ ለምን አንጨክንም? እግዚአብሔርን ከረዳቶቻችን እንደ አንዱ ለምን እናየዋለን? ከመታመኛዎቻችን እንደ አንዱስ ለምን እንቆጥረዋለን? ከተስፋዎቻችንስ እንደ አንዱ ለምን ይሆናል?
ኧረ ተስፋ ያልነውን ነገር ሁሉ ዛሬ እግዚአብሔር ያስጥለንና፣ በውሃው ላይ መራመድ ይሁንልን!
ከአብርሃም ጋር ያደረገውን ኪዳን፣ ለይስሐቅም በመሐላ የተሰጠውን ተስፋ አይረሳም። መዝ 105:9
አባትዬ እባክህ ብቻህን በሕይወታችን ላይ ታይ። አንተን ብቻ መታመን ይሁንልን? ሰምተህኛልና ተባረክልኝ።
---------
እለታዊ ዲቮሽኑ ሊጠናቀቅ 35 ቀን ቀረው
መቼም ይህ ድብልቅልቁ የወጣበት ዘመን፣ ከእግዚአብሔር ይልቅ ብዙ ሌሎች 'ተስፋዎቻችንንና እና ረዳቶቻችንን' እያስቆጠረን ነው። በአይነትም በብዛትም እጅግ በርካታ ስለሆኑ እነሱን ሁሉ እዚህ መጥቀስ አይቻልም። እኔም እናንተም እናውቃቸዋለን እኮ!!!! ለቁጥር የሚያዳግቱ 'ረዳቶቻችን እና ተስፋዎቻችን' በዙሪያችን አሉ።
እንዲያው እነዚህ የተደገፍናቸው ነገሮች ሸንበቆ ሲሆኑብን፣ “የሚረዳኝ የለምና ከእኔ አትራቅ፣ አሁንስ ተስፋዬ ማነው? እግዚአብሔር አይደለምን?፣ ወይም በሰው ከመደገፍ በእግዚአብሔር መደገፍ ይሻላል፣ ወ.ዘ.ተ. የሚሉ እንጉርጉሮ አዘል ጥቅሶችን ለይምሰል ያህል እንጠቀማለን።
ግን ሕይወታችን እኮ የሚቀናበረው እግዚአብሔር እንዳለው ነው እንጅ፣ በደገፋዎቻችንን ብዛት እንዳልሆነ የየግል ሕይወታችን ምስክር ነው። ስንቱ የተደገፍንበት መንገድ ላይ እየቀረ እኮ ባላስልጣኑ ኢየሱስ ብቻ ዛሬም ነገም ለዘላለምም ከእኛ ጋር ይዘልቃል።
ስለዚህ፣ ለምን አንጨክንም? እግዚአብሔርን ከረዳቶቻችን እንደ አንዱ ለምን እናየዋለን? ከመታመኛዎቻችን እንደ አንዱስ ለምን እንቆጥረዋለን? ከተስፋዎቻችንስ እንደ አንዱ ለምን ይሆናል?
ኧረ ተስፋ ያልነውን ነገር ሁሉ ዛሬ እግዚአብሔር ያስጥለንና፣ በውሃው ላይ መራመድ ይሁንልን!
ከአብርሃም ጋር ያደረገውን ኪዳን፣ ለይስሐቅም በመሐላ የተሰጠውን ተስፋ አይረሳም። መዝ 105:9
አባትዬ እባክህ ብቻህን በሕይወታችን ላይ ታይ። አንተን ብቻ መታመን ይሁንልን? ሰምተህኛልና ተባረክልኝ።
---------
እለታዊ ዲቮሽኑ ሊጠናቀቅ 35 ቀን ቀረው
No comments:
Post a Comment