Saturday, August 29, 2015

ተኛሁ፣ አንቀላፋሁ!!!!

ዲቮሽን 354/07፥ እሁድ፥ ነሐሴ 24/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)


ተኛሁ፣ አንቀላፋሁ!!!! እኔ ተኛሁ፣ አንቀላፋሁም እግዚአብሔር ደግፎኛልና ነቃሁ። መዝ 2፡5 ዳዊት ምንም የሚያስተኛ ነገር ሳይኖር እኮ ነው እንዲህ ያለው። ያውም መንግስትን ያህል ነገር በገዛ ልጁ ተነጥቆ በባዶ እግሩ እየተንከራተተ እኮ ነው፣ ለጥ ብሎ የተኛው! ያውቀዋላ! እግዚአብሔርን ማን መሆኑን ጥንቅቅ አድርጎ ያውቀዋላ! ሽብር እና ድንጋጤ ቢበዛም፣ የሚያባንን እና የሚያስቃዥ ነገር በዙሪያችን እያለ ለጥ አድርጎ የሰላም እንቅልፍ የሚሰጠን ጠባቂያችን እግዚአብሔር ብቻ ነው። ትጉህ እረኛ፣ አይተኛ አያንቀላፋ! አይደክመው አይታክተው! የእኛ እግዚአብሔር ከሁሉ በላይ ነው። ከሳኦልም ከአቤሴሌምም በላይ ነው። ከተቃዋሚዎቻችን ሁሉ በላይ ነው። እረ አንተ የሁሉ የበላይ ነህ እንበለው ወዳጆቼ!!! ሰይጣን እኮ የተጣለ ነው:: እንዴት ሰይጣንን፣ ሟርተኛን፣ ጠንቋይን፣ አስማተኛን ፈርተን ዓይናችን ፈጦ ያድራል! እንዴት በሽታን፣ ህመምን፣ ድህነትን ፈርተን ስንባንን እናድራለን! የስከዛሬው ይበቃቸዋል። ከሳሻችን የተጣለ የተወረወረ ነው!!!!! ስለዚህ በሰላም እንኖራለን፣ እንወጣለን እንገባለን፣ እንተኛለን። ተኝተን ራእይ እናያለን። ድንጋጤ፣ ፍርሐት፣ ቅዥት የሚባል የለም!!! ወንጌላችን ደግሞ አያረጅም፣ ፋሽን እኮ አይደለም አንድ ወቅት የምናምርበት ሌላ ጊዜ የሚያልፍበት!!! በሰላም እተኛለሁ፣ አንቀላፋለሁም፣ አቤቱ አንተ ብቻህን በእምነት አሳድረህኛልና። መዝ 4፡8 --------- ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 12 ቀን ቀርቶታል

No comments:

Post a Comment