Thursday, August 27, 2015

እግዚአብሔር ዓዋቂ ነው!!!!

ዲቮሽን 352/07፥ አር፥ ነሐሴ 22/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)


እግዚአብሔር ዓዋቂ ነው!!!!


እግዚአብሔር አዋቂ ነውና፣ እግዚአብሔር ሥራውን የሚመዝን ነውና:: 1ኛ ሳሙ 2:3


እንግዲህ እግዚአብሔር አዋቂ ነው ስንል ምን እያልን ነው? ከወር ከሁለት ወር በኋላ የሚሆነውን ያውቃል እያልን ነው? ወይስ ከተወለድን እንደምናድግ፣ ካደግንም ሥራ እንደምንይዝ፣ ስራ ከያዝንም እንደምናገባ፣ ካገባንም እንደምንወልድ ያውቃል ማለት ነው? ወይስ ከታመምን መድሃኒታችንን ባግባቡ ከወሰድን እንደምንድን ያውቃል ማለት ነው? ወይስ ጠዋት ተነሰቼ ቤተክርስትያን እንደምንሔድ ያውቃል ማለት ነው? ወይስ በፍርድ ቤት የያዝነውን ክርክር እንደምንረታ ያውቃል ማለት ነው? ወይስ ፈተናችንን በርትተን ካጠናን እንደምናልፍ ያውቃል ማለት ነው? አ-ይ-ደ-ለ-ም!!!


እግዚአብሔር አዋቂ ነው ስንል፡ ዓልፋ እና ዖሜጋ ነው ማለታችን ነው። የእኛን ብቻ አይደለም የመሠረታትን የዓለምን እና በውስጧ ያለውን ነገር አካሔድ ገና ጥንት ያውቀዋል ማለት ነው። እረ ገና እናትና አባታችን ሳይተዋወቁ፣ ሊጋቡም ሊዋለዱም ሳያስቡን እግዚአብሔር ያውቀናል!!! ስንቱን ልንገራችሁ! ብቻ በዚህች ዓእምሮአችን የእግዚአብሔርን አዋቂነት መተንተን አንችልም። ሞኝ ብቻ ነው ቸኩሎ፡ እግዚአብሔር የለም የሚለው። ሰነፍ ብቻ ነው፣ በአፉ ፈጥኖ እግዚአብሔር የለም እያለ በፊዚክስና እና በጂኦሜትሪ ሊያስቀምጥ የሚቸኩል!!!!



አልቃሻዋን ሐና ዘማሪ፣ ጭምቷን ሳራ ሳቂታ፣ ጨቅጫቃውን አብርሐም የብዙሃን አባት፣ ተጠራጣሪውን ዘካርያስ የመንገድ ጠራጊው አባት ያደረገውን እግዚአብሔር እንግዲህ በምን እንመስለዋለን!



ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፣ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፣ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤ በማዳንህ ደስ ብሎኛል።1ሳሙ 2፡1 --------- ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 14ቀን ቀርቶታል

No comments:

Post a Comment