ዲቮሽን 325/07፥ ቅዳሜ፥ ሐምሌ 25/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
እግዚአብሔር ብቻውን!!!!!
እግዚአብሔር ብቻ መራው፣ ምንም ባዕድ አምላክ አብሮት አልነበረም። ዘዳግም 32፡12
ያዕቆብ በበረሐ ሲንከራተት፣ ያች የመከረችው እማዬ እንኳን አጠገቡ የለችም። የገዛ ዘመዱ ላባ፣ እንደዚያ አሥር ጊዜ ሲጫወትበት ማን አጠገቡ ነበር? ማ--ን----ም! ያዕቆብን የመራው፣ አትፍራ እያለ ያበረታው፣ የባረከው፣ ያበለጸገው እኮ አንድ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ራሱ ያዕቆብ እኮ ይመሰክራል፣ ዮርዳኖስን ስሻገር በእጄ ከነበረው በስተቀር ምንም አልነበረኝም፣ አሁን ግን ይኸው ሰራዊት ሆኛለሁ! (ዘፍ 32፡10) እያለ ይመሰክራል።
በመንገደችን ሁሉ፣ ከስኬታችን ጀርባ፣ ከዛሬው ማንነታችን ጀርባ ያለው አንድ እግዚአብሔር ብቻ ነው።
አስተውላችሁ እንደሆነ እኮ፣ ቃል ብቻ ስላለን ነው በሕይወት ያለነው፣ የበዛነው፣ የተትረፈረፍነው። ጠላት ለእኛ ጉድጓድ ሳይቆፍር ቀርቶ መሰላችሁ? ጠላት ባሪያው ሊያደርገን፣ ሊያርደን፣ ሊሰርቀን፣ ሊያጠፋን እኮ፣ ዙሪያችንን እንደሚያጓራ አንበሳ እየጮኸ ሲያስፈራራን ነበር። ግን፣ የእኛ መሪ እግዚብሔር ከለከለው።
አንዴ በበሽታ፣ አንዴ በሟርት፣ አንዴ በድግምት፣ አንዴ በማጣት፣ አንዴ ሕብረታችንን በመበተን፣ አንዴ መላ ሕይወታችንን በማወክ፣ አንዴ ባዕድ አማልክትን እንድናመልክ በማድረግ፣ እረ ስንቱ! ሊጫወትብን እኮ አካሔዱን እየቀያየረ ፈትኖናል።
ለእኛ ግን መሪያችን፣ አንድ እግዚአብሔር ነው። አዳኛችን አንድ እግዚአብሔር ነው።
ስለዚህ፣ ቃሉ እንደሚለን፣ "አምርረህ በተነሣህ ጊዜ ግን፣ ቀንበሩን ከጫንቃህ ላይ ወዲያ ትጥላለህ" እንዳለ (ዘፍ 27፡40)፣ አምርረን ተነስተናል።
ጠላት ይህን ይወቅ!!!!! ሰይጣን ይስማ፣ ሁሉም ይስማ፣ የሚመለከተው ሁሉ ይስማ!!!! መሪያችንን እግዚአብሔርን ብቻ እናመልካለን!!! ሳይኮሎጂ አናመልክም፣ ፊሎሶፊ አናመልክም! ዓለምንና በውስጧ ያለውን አናመልክም!!!!!! 666ን አናመልክም!!!!! ይህ ግልጽ አቋማችን ነው!!!!!!!!!!!
እግዚአብሔር ብቻውን መሪ ነው!!!!!!!!!!
--------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 41 ቀን ቀርቶታል
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 41 ቀን ቀርቶታል
No comments:
Post a Comment