ዲቮሽን 324/07፥ አርብ፥ ሐምሌ 24/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
ባያድነንስ??? እሰይ! አያድነና!!!!!
ነገር ግን ንጉሥ ሆይ፣ ባያድነንም እንኳ አማልክትህን እንደማናገለግል፣ ላቆምኸውም የወርቅ ምስል እንደማንሰግድ ዕወቅ። ዳን 3፡18
እነአናንያ፣ ሚሳኤልና አዛርያ ያ የሚንበለበለው የእቶኑ እሳት ምንም ሳይመስላቸው፣ ልክ የመዋኛ ገንዳ ውስጥ የመግባትና የመዝናናት ያህል የቀለለባቸው የዘላለም ጉዳይ ስለገባቸው ነው።
ወገኖቼ አነግራችኋለሁ፣ የዘላለም ሕይወት የሚባል ነገር አለ። አንዳንዴ የት ጋ ነው ብኩርናችንን የጣልነው ብላችሁ አስባችሁ ታውቃችሁ? ነገሩ የመጣው እኮ ቀስ በቀስ ነው። ሰዎች መጥተው፣ ጌታ ምን አደረገልሽ/ምን አደረገልህ? ሲሉን እኛም የራሱ ፋንታ ብለን፣ "ጌታን ጌታን" ማለቴ ምን ጠቀመኝ ብለን አይደል እንዴ ከዓለም የአኗኗር ዘይቤ ጋር የተመሳሰልነው? በቤተክርስትያናችን ውስጥ እንግዳ ትምሕርቶች ሲጀመሩ፣ የዘመን ፍጻሜ ደወል እየተደወለ መሆኑን መች አስተዋልን? ትምህርታቸው እንደማይሽር ቁስል ይሠራጫል፣ 2ጢሞ 2፡17 የተባሉት መምህራንን ፓ! ፓ! ፓ! እያልን እያጨበጨብን፣ እልል እያልን እኛም የነሱ ደቀመዝሙሮች መሆናችንን መች ልብ አልን?
እግዚአብሔር ባያድነንስ? ከበሽታችን ባይፈውሰንስ? ባል/ሚስት/ልጅ ባይሰጠንስ? ሥራ፣ ገንዘብ፣ መኪና፣ ቤት፣ ባይሰጠንስ? በቃ በምድር ላይ ባይሳካልንስ? በቃ!!! ከሞት የሚቀር አለ እንዴ!? ማነው በዝናው፣ በሥልጣኑ፣ በሐብቱ ልክ በምድር ላይ ጸንቶ የኖረ? ማንም የለም። በዚች ህይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ ከሰው ይልቅ ምስኪኖች ነን ያለው ጳውሎስ፣ 1 ቆሮ 15፡ 19 የዘላለም ነገር ስለገባው ነው።
ወዳጄ ሆይ፣ መልሰን እኛም እንመለሳለን፤ ማረን፣ ይቅር በለን። ሰምተህኛልና ተባረክልኝ ኢየሱስ።
--------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 42 ቀን ቀርቶታል
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 42 ቀን ቀርቶታል
No comments:
Post a Comment