Thursday, July 30, 2015

ይጨምርልን !

ዲቮሽን 323/07 ፤ ሓሙስ ሓምሌ 23 /07
( ወንድም ጌታሁን ሓለፎም )


ይጨምርልን !


“ ምህረት እና ሰላም ፍቅርም ይብዛላችሁ ” ይሁዳ 1፡- 2


አሜን ይብዛልን !


መቼስ ሁላችንም እንደምንመሰክረው እና እንደምንረዳው ፡- ወደ ጌታ ዘውር ካልንበት ጊዜ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ ከእግዚአብሔር ከሆነልን አስደናቂ በረከቶች ውስጥ አንዳንዶቹን እንቁጠር ብለን ብንል ፤ የተትረፈረፉልን ሰላም ምህረትና ፍቅር ከብዙዎቹ ጥቂቶቹ ሆነው እናገኛቸዋለን ፡፡



እንደበግ የምንቅበዘበዝ ፤እረፍት አጥተን የምንባዝን ነበርን ፤ ነገር ግን ጌታ ወደ ሂወታችን ሲገባ ታላቅ ሰላም እና ምረጋጋትን ተቀበልን ፤ በነጻነት መግባት መውጣት ሆነልን ፤ መሲሁ ወደ ልባችን እልፍኝ ሰላምን ይዞ መጣ !



በመስቀል ላይ ስለ ሰው ልጆች ኃጢያት እራሱን አሳልፎ በሰጠው በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል ታላቅ የሆነውን የእግዚአብሔርን ፍቅር አየን !



ታዲያ ሓዋርያው ያቆብ እንደሚለን እነኝህ ከግዚአብሔር የተሰጡን ስጦታዎች ዋጋቸው ታላቅ ነው እና ፤ በየእለቱ የሚበዙ የሚያድጉ የሚጨምሩ ይሁኑ እንጅ በነገሮች እና በሁኔታዎች የተነሳ የሚከስሙና የሚጫጩ መሆን የለባቸውም ፤ ተመልሰን ወደ ፍርሃት ፤ ተመልሰን ወደድንጋጤ ተመልሰን ወደ ኃጢያት እስራት ፤ ተመልሰን ወደብዝበዛ እና ሽንፈት መግባት አይገባንም ፤ይልቁንም የሚበዙ የሚጨምሩ እና የሚያድጉ ይሁኑ !




እውነት ነው ይህ ከጌታ የተሰጠን በረከት በየእለቱ የሚበዛ እና የሚጨምር መሆን ይገባዋል ፤ በነጻ ከእግዚአብሔር የተቀበልነው ነገር ግን እጅግ ውድ ስጦታ ! የማይከፈልበት ያልተለፋበት ነጻ በረከት! አዎ ብር ወርቅ የማይገዛው ውድ ስጦታ !



ስለዚህም ፡- በወንድሞች መካከል ሰላም ይሁን !

ለቤተክርስቲያን ፤ ለምድራችን ፤ ለአለም ሰላም ይሁን ! 



ለሰው ልጆች በሙሉ ከእግዚአብሔር ምህረት እና ሰላም ፍቅር ይሁን ! መጭው ዘመናችን “ ምህረት፤ሰላም እና ፍቅር ” የሚበዛበት ወደ ጌታ ነፍሳት የሚጨመርበት በነገር ሁሉ የምናድግበት ዘመን ይሁን !


------------
እለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ሊጠናቀቅ 43 ቀናቶች ቀርተውታል !

No comments:

Post a Comment