ዲቮሽን 298/07፥ እሁድ፥ ሰኔ 28/07 ዓ/ም
(በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)
(በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)
ሁሉ – ለማነጽ ይሁን !
እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ምንድር ነው? (ምን እንበል?) በምትሰበሰቡበት ጊዜ … ሁሉ ለማነጽ ይሁን(1 ቆሮ 14፡26)።
በብዙ ምክንያቶች ስብሰባ እናደርጋለን፡፡ በቤተሰብ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር – ለመመካከር፣ በቤተክርስቲያን ጉዳይ ላይ ለመነጋገር – ለመመካከር፣ በቤተእምነት ጉዳይ ላይ ለመነጋገር – ለመመካከር፣ በሀገር ጉዳይ ላይ ለመነጋገር – ለመመካከር፣ ልዩ ልዩ ዓይነት ስብሰባ እናደርጋለን፣ በተለያዩ ጉባዔዎች ላይ እንቀመጣለን፡፡
ወገኖች ሆይ፣ የአጥቢያ ቤተክርስቲያን ውስጥ የሽማግሌዎች ስብሰባ፣ የዲያቆናት ስብሰባ፣ የኮሚቴ ስብሰባ፣ የጸሎት ኅብረት ስብሰባ፣ የመዘምራን ስብስባ፣ የቤት ለቤት ኅብረት ስብሰባ፣ የወጣቶች ስብሰባ፣ የባለትዳሮች ስብሰባ፣ ሌሎችም ከሕጻናት እስከ ዐዋቂ ብዙ ዓይነት ስብሰባዎች እናደርጋለን፡፡
ወገኖች ሆይ፣ ማናቸውም ዓይነት ስብሰባ ይሁን፣ ብቻ በምንሰበሰብበት ጊዜ አንድ መሠረታዊ መርህ መጠበቁን እናስተውል – ሁሉ ለማነጽ ይሁን! በቃለጉባኤያችን ሁሉ፣ በውይይት ጊዜያችን ሁሉ፣ በድምጸ ውሳኔያችን ሁሉ፣ በአቋም መግለጫችን ሁሉ … ይህ መርህ መጠበቁን እናስተውል – ሁሉ ለማነጽ ይሁን!
ወገኖች ሆይ፣ ስንሰብክ–ስናስተምር፣ ስንጽፍ–ስናሳትም፣ ስንነግድ–ስናተርፍ፣ ስናወራ–ስንሰማ፣ ስንወርድ–ስንወጣ … ይህ መርህ መጠበቁን እናስተውል – ሁሉ ለማነጽ ይሁን!
------------------
------------------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6 ቀን 2007 ላይ ይጠናቀቃል፡፡ በዚህ ዓመት ብቻ ዲቮሽኑን የሚከታተሉ ከ15000 በላይ ሰዎች ከመላው ዓለም ማፍራት ተችሏል፡፡ ዲቮሽኖቹ፣ ሰዎች ወደጌታ እንዲመጡ፣ በርካታዎቹም ከውድቀታቸው እንዲነሱና ከስብራታቸው እንዲጠገኑ፣ በርካታዎቹም እንዲታነጹ …ምክንያት ሆነዋል፡፡ ክብሩን ሁሉ ጌታ ይውሰድ፡፡
እነዚህን ዲቮሽኖች ሰብስቦ በአንድ መጽሐፍ ላይ ለማሳተምና መስከረም 2008 ዓ.ም. ላይ ለአንባቢዎች ለማድረስ እንቅስቃሴ ተጀምሯል፡፡
በሀገራችን ታሪክ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውንና አንድም ቀን ሳይቋረጥ ዓመቱን ሙሉ ለአንባቢዎች ይቀርብ የነበረውን፥ እንዲሁም በርካታ ነጻ አስተያየቶች ሲሰጡበትና በርካታ ቅዱሳን ሲጸልዩለት የቆዩትን ይህን የጥሞና መጽሐፍ ሁሉም የዲቮሽኑ ተከታታዮችና ሌሎችም ሊያገኙት ይገባል የሚል ራዕይ ተይዟል፡፡
ይህን ታሪካዊ መጽሐፍ፣ የማሳተሚያ ወጭ በገንዘብ ለመደገፍ የምትፈልጉ፣ ወይም ገፆች በመግዛት በመጽሐፉ ላይ የድርጅታችሁንና የአገልግሎታችሁን ዓላማዎች ለአንባቢያን ማስተዋወቅ የምትፈልጉ፣ ምርቶቻችሁንና ማናቸውንም አገልግሎታችሁን በማስታወቂያ ማስተላለፍ
የምትፈልጉ በሀገር ውስጥና ውጭ የምትገኙ ወገኖች ሁሉ ባሉን ውስን ገጾች ውስጥ ቦታ አስቀድሞ በመያዝ ራዕዩን መደገፍ ትችላላችሁ፡፡
የምትፈልጉ በሀገር ውስጥና ውጭ የምትገኙ ወገኖች ሁሉ ባሉን ውስን ገጾች ውስጥ ቦታ አስቀድሞ በመያዝ ራዕዩን መደገፍ ትችላላችሁ፡፡
ሁሉም የዲቮሽኑ ተገልጋይ የነበራችሁ አነሰ በዛ ሳትሉ በዲቮሽኑ የተባረካችሁ መሆኑን የሚያሳይ የፍቅራችሁን ስጦታ ልታበረክቱ ትችላላችሁ፡፡ ለዚህ ጥሪ የምትመልሱት የፍቅራችሁ ምላሽ፥ ለቀጣዩና ጌታ በልቤ ያስቀመጠውን ለየት ያለ አገልግሎት ወደእናንተ ይዤ እንድመጣ የበለጠ የሚያነሳሳኝ መሆኑንም አትርሱ፡፡ ዓመቱን ሙሉ በዲቮሽኑ ስትባረኩበት ነበር፥ አሁን ደግሞ እኔን ለመባረክ ተራውና ዕድሉ ወደእናንተ ቀርቧልና ተጠቀሙበት፡፡ ጌታ ይባርካችሁ፡፡
ለተጨማሪ መረጃ፣ በሞባይል መደወል ይቻላል፡፡ ዓመቱን ሙሉ አብራችሁን ለነበራችሁ ወገኖች ሁሉ ከፍ ያለ ምስጋናዬን አቀርባለሁ፡፡ በዲቮሽኑ መቆም ልባችሁ ለሚያዝንብን ወገኖች ደግሞ ከፍ ያለ ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡ ጌታ ይባርካችሁ፡፡ የናንተው አገልጋይ፥ ፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ
No comments:
Post a Comment