ዲቮሽን 310/07፥ አርብ፥ ሐምሌ 10/07 ዓ/ም
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
እናስለምድ!!!!
እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ። 2 ጢሞ 4፡7
በዚህ በመጨረሻው ዘመን ዓለምን ለመምሰል ደፋ ቀና በማለት ስንደክም እንውላለን። በዓለም ያለው ሁሉ እንዳይቀርብን፣ ራሳችንን እናተጋለን። በዓለም ያሉትን ከመማረክ ይልቅ እኛ ራሳችን በእነሱ ተማርከን፣ በቤተክርስትያናችን፣ በቤተሰባችን፣ በሥራ ቦታችን፣ በአገልግሎታችን፣ በማሕበራዊ ሕይወታችን . . . ያለንን የሞያም ሆነ የገንዘብ ዓቅም አሟጠን ዓለምን ለመምሰል በልዩ ብርታት ስንሠራ እንገኛለን። የዓለም እውቀቶች በቤተክርስትያናችን እና በቤተሰባችን ላይ ሠርገው ገብተው፣ እምነት እና ስነልቦና ተምታቶብን፣ እንደዘመኑ ለመሆን የማንፈነቅለው ድንጋይ የለም። አሳዛኙ ነገር ደግሞ፣ ለምናደርገው ነገር ሁሉ ተስማሚ ጥቅስ ከመጽሐፍ ቅዱሳችን ማግኘታችን ነው።
መጽሐፍ የሚለን ግን፣ “እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ” ነው። አሁን ያለንበት ይህ የማብቂያው ዘመን፣ ለሁላችንም እጅግ አዳጋች እና ፈታኝ መሆኑ የማይካድ ሀቅ ነው። ግን የሚያዋጣው እግዚአብሔርን መምሰል ነው። እግዚአብሔርን መምሰል ማለት ምን ማለት ነው? ለሚለው መጽሐፍ ቅዱስ ምላሽ ስለሚሰጠን፣ ወደ ቀድሞው ፍቅራችን፣ የዋህነታችን፣ ትህትናችን፣ እውነተኛታችን፣ ገራገርነታችን ተመልሰን፣ በፍጹም ንስሐ ወደ ቃሉ እንመለስ።
አባት ሆይ፣ ሁልጊዜም ቢሆን ስለማትሰለቸን ተመስገን። በዓለምና በውስጧ ባሉት ነገሮች መማረካችን፣ መፍዘዛችን፣ መወሰዳችን እውነት ነው፤ ቢሆንም ግን፣ ዋጋ የከፈልክብን ልጆችህ ስንጠፋ ዝም አትበለን። አንተን ለመምሰል፣ እለት እለት እራሳችንን ለማስለመድ እንፈልጋለን። ስለዚህ ዛሬ ጸጋህ ይደግፈን፣ አሁን መንፈስህን ላክልንና እባክህ ወደመገኘትህ አስገባን? ሰምተህኛልን ተባረክ።
--------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 56 ቀን ቀርቶታል፡፡
(በእህት ማርታ ሲሳይነህ)
እናስለምድ!!!!
እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ። 2 ጢሞ 4፡7
በዚህ በመጨረሻው ዘመን ዓለምን ለመምሰል ደፋ ቀና በማለት ስንደክም እንውላለን። በዓለም ያለው ሁሉ እንዳይቀርብን፣ ራሳችንን እናተጋለን። በዓለም ያሉትን ከመማረክ ይልቅ እኛ ራሳችን በእነሱ ተማርከን፣ በቤተክርስትያናችን፣ በቤተሰባችን፣ በሥራ ቦታችን፣ በአገልግሎታችን፣ በማሕበራዊ ሕይወታችን . . . ያለንን የሞያም ሆነ የገንዘብ ዓቅም አሟጠን ዓለምን ለመምሰል በልዩ ብርታት ስንሠራ እንገኛለን። የዓለም እውቀቶች በቤተክርስትያናችን እና በቤተሰባችን ላይ ሠርገው ገብተው፣ እምነት እና ስነልቦና ተምታቶብን፣ እንደዘመኑ ለመሆን የማንፈነቅለው ድንጋይ የለም። አሳዛኙ ነገር ደግሞ፣ ለምናደርገው ነገር ሁሉ ተስማሚ ጥቅስ ከመጽሐፍ ቅዱሳችን ማግኘታችን ነው።
መጽሐፍ የሚለን ግን፣ “እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ” ነው። አሁን ያለንበት ይህ የማብቂያው ዘመን፣ ለሁላችንም እጅግ አዳጋች እና ፈታኝ መሆኑ የማይካድ ሀቅ ነው። ግን የሚያዋጣው እግዚአብሔርን መምሰል ነው። እግዚአብሔርን መምሰል ማለት ምን ማለት ነው? ለሚለው መጽሐፍ ቅዱስ ምላሽ ስለሚሰጠን፣ ወደ ቀድሞው ፍቅራችን፣ የዋህነታችን፣ ትህትናችን፣ እውነተኛታችን፣ ገራገርነታችን ተመልሰን፣ በፍጹም ንስሐ ወደ ቃሉ እንመለስ።
አባት ሆይ፣ ሁልጊዜም ቢሆን ስለማትሰለቸን ተመስገን። በዓለምና በውስጧ ባሉት ነገሮች መማረካችን፣ መፍዘዛችን፣ መወሰዳችን እውነት ነው፤ ቢሆንም ግን፣ ዋጋ የከፈልክብን ልጆችህ ስንጠፋ ዝም አትበለን። አንተን ለመምሰል፣ እለት እለት እራሳችንን ለማስለመድ እንፈልጋለን። ስለዚህ ዛሬ ጸጋህ ይደግፈን፣ አሁን መንፈስህን ላክልንና እባክህ ወደመገኘትህ አስገባን? ሰምተህኛልን ተባረክ።
--------
ዕለታዊ ዲቮሽኑ ጳጉሜ 6/07 ዓ/ም ይጠናቀቃል፡፡ አሁን 56 ቀን ቀርቶታል፡፡
No comments:
Post a Comment