Sunday, June 7, 2015

በፍጹም አልጥልህም!!!!!!!

ዲቮሽን 271/07 ሰኞ ሰኔ 1/07
(
በእህት ማርታ ሲሳይነህ)

በፍጹም አልጥልህም!!!!!!!


እርሱ ራሱ አልለቅህም፣ ከቶም አልተውህም ብሎአልናዕብ 13 5

እንግዲህ ጌታን፣ ካንተ ወዴት እንሄዳለን? ስንለው፣ የእርሱ ምላሽ የዘላለም ጥም ቆራጭና የማያንቀዠቅዥ ይሆናል። በመከራ መካከል ብንሄድ እንኳን እርሱ ህይወታችንን ይጠብቃታል። በጠላቶቻችን ቁጣ ላይ እጁን ይዘረጋል፣ በቀኝ እጁም ያድነናል። ሰይጣን፣ ሊገድለን ሲያደባ፣ ከብዙ ሞቶች ጌታ ታድጎናል። በአጠገባችን ሺህ፣ በቀኛችን አስር ሺህ ሲወድቅ፣ ከብርቱዋ ከጌታ እጅ የተነሳ በህይወት ኖርን።

እርሱ ራሱ፣ ጌታ በገዛ አንደበቱአልለቅህም፣ ከቶ አልተውህም፣ በፍጹም አልጥልህም፣ስላለን እነሆ ዛሬ የሱን ማዳን ለማውራት ባለ ተራዎች ሆነናል። በተባረክነው ልክ ልንባርክ፣ የጠፉትን ፈላጊ ያዘኑትን አጽናኝ ልንሆን፣ የዛሉትን ልናበረታ፣ ወንጌልን በዓለም ዙሪያ እስከ ምድር ዳርቻ ለማድረስ እድለኞች ሆንን። ምክንያቱም፣ እርሱ ራሱ፣ አልጥላችሁም ስላለን!

ጌታ፣ እርሱ ራሱ፣ አልተዋችሁም ስላለን፣ ‹‹አድነን›› ባልነው ጊዜ፣ ጩኸታችንን ስለሰማልን፡ ስለራራልን፣ ከምናውቀውና ከማናውቀው፣ ከምንገምተውና ከማንገምተው ውርደት እና ጉድ ሁሉ ጠብቆን፣ እነሆ ዛሬን ለማየት በቃን።

አባት ሆይ፣ የልመናችንንን ድምጽ ሰምተሀልና እንወድሀለን፤ ጆሮህን ወደ እኛ አዘንብለሀልና በህይወት ዘመናችን ሁሉ ስምህን እንጠራለን (መዝ 116) አላሳፈርከንም፣ ሞት ሲገባን ህይወትን ሰጠህን፣ ውርደት ሲጠብቀን በክብር አቆምከን፣ መጠጊያ እና መሸሸጊያ ሁነን ባልንህ ጊዜ ሁሉ ከጠላት ክፋትና አመጻ ሰውረህናልና ተባረክ። ምስጋናችን ወደ ማደሪያህ ይግባ። እንወድሀለን።

ትምህርቱ ጠቅሞዎታል? እንግዲያውስ እባክዎ ላይክ እና ሼር ያድርጉ፣ ጌታ ይባርክዎ!!!

No comments:

Post a Comment