Wednesday, May 27, 2015

የማይነቀፍ ንግግር



ዲቮሽን 259/07 ረቡዕ፣ ግንቦት 19/07
(
በወ/ም አበባዬ ቢተው)


የማይነቀፍ ንግግር

".....የማይነቀፍ ንግግርን ግለጥ።" (ወደ ቲቶ 2:8)

የምናመልከው እና የምንከተለው ኢየሱስ እውነት እና እውነተኛ ነው። (ዮሐ 146) የተናገራቸው እና አሁንም የሚናገራቸው ቃላት እውነት ናቸው።(ዮሐ 1717)

እኛ ክርስቲያኖች ደግሞ የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ስንሆን የእርሱ ልብ ያለን እና እርሱን ልንመስል የተገባን ነን።( 1ቆሮ 216 111)

ስለዚህ ልክ የጌታችን ንግግር እና ቃላት ነቀፋ የማይገኝባቸው እንደሆኑ ሁሉ የእኛም እንዲሁ መሆን አለበት። ሰዎችን የማያንፅ እና የማይጠቅም ክፉ ንግግር ከእኛ በማንኛውም መንገድ ሊወጣ አይገባም። በሐሜት እና አሉባልታ ተጠምደን ራሳችንን ስናሳድፍ እና የሌሎችን ሕሊና ስናቆሽሽ ልንገኝ አይገባም።

ለሻይ ቡና ስንቀመጥ፡ እንደ ፌስ ቡክ ያሉ ማህበራዊ ድህረ ገፆችን ስንጠቀም፡ ሌሎችን ስናገለግል የምንናገረው ንግግር የማይነቀፍ መሆኑን እናረጋግጥ! ስለ ቤተ ክርስቲያን፡ ፖለቲካ፡ እና ግለሰቦች ባላየነው እና ባልገባን ነገር እየገባን የምንናገረውን እና አስረግጠን የምናስረዳውን ነገር (1 ጢሞ 17) ከሐሜት እና አሉባልታ የፀዳ የማነቀፍ መሆኑን እናረጋግጥ! ተጨባጭነት የሌላቸው ከንቱ ንግግሮቸ እንዳይሆኑ እንፍራ። የክርስትና ስነ ምግባር ግድ ይለናልና።

ንግግራችን አማኞችን ተጠራጣሪ፡ የዋሆችን ክፉ፡ ቅኖችን ጠማማ፡ ሰላማዊዎችን፡ አመፀኛ፡ ቸር እና ሩህሩሆችን፡ ጨካኛ እንዳያደርግ እንፍራ! የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናልና!

ሐሜት፡ አሉባልታ፡ እና ነቀፋ ያለባቸው ንግግሮች መንፈሳዊ ንፅህናችንን ከማሳደፍ በላይ መንፈስ ቅዱስ በእኛ እንዳይሰራ ይከለክላል እና እንጠንቀቅ! (ኤፌ 429-30)

ጌታ ማስተዋል ይጨምርልን! " ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ።" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4:29)
ትምህርቱ ጠቅሞዎታል? እንግዲያውስ እባክዎ ላይክና ሼር ያድርጉ፣ ጌታ ይባርክዎ።

No comments:

Post a Comment