Thursday, April 9, 2015

'ክራ-ላይሶ' – ማረን አቤቱ!




ዲቮሽን 211/07 ሐሙስ፣ ሚያዝያ 1/07 /
(
በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)

'ክራ-ላይሶ' – ማረን አቤቱ!


…መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል …. ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም (ዮሐ 1011 1225)
'ክራ-ላይሶ' (ኪሪዬ ኤሊይሶን) – ማረን፣ አቤቱ ማረን!

ፍርዳችንን የወሰድኸው፣ መስቀልን የተሸከምኸው፣ ከሞትም ኃይል ያወጣኸን፣ ኦ የሞትህልን አድነን፣ ስማልን ጸሎታችንን፡፡ 'ክራ-ላይሶ'!

ታላቅ ሥራህ ተፈጸመ፣ ፍርድ ምሕረቱን አተመ፣ የፍርድ አምላክ ለኃጢአት፣ ከሰጠ በቂውን ቅጣት፣ መሐሪ አምላክ ልጆቹ፣ አደረገን በምሕረቱ፡፡ 'ክራ-ላይሶ'!

እኛ ፍጹም ደካሞች ነን፣ ጌታ ኢየሱስ ሆይ አበርታን፣ በምሕረት እጅህ ደግፈን፣ በቅዱስ መንፈስህ እርዳን፣ ያምላክ ልጆች ያደረግኸን፣ የሱስ ክርስቶስ ሆይ ተመስገን፡፡ 'ክራ-ላይሶ'!

አትራቅብን የሱስ ሆይ፣ ሁልጊዜ ከእኛ ዘንድ ቆይ፣ በፈተና አበርትተህ፣ በትግልም አጠንክረህ፣ በሕይወትም በሞትም ጻር፣ በደምህ ኃይል ሁን ከኛ ጋር(ስብሀት ለአምላክ ፷፩)፡፡

አቤቱ የፍቅርና የምሕረት ጌታ፣ ኪሪዬ ኤሊይሶን – ማረን አቤቱ ማረን!!

አንተ ነፍስህን ለእኛ ለበጎችህ ያኖርኸው፣ 'ክራ-ላይሶ'!  አንተ መልካም እረኛ፣ 'ክራ-ላይሶ'! ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውምና፣ 'ክራ-ላይሶ'!  ለዚህ ፍቅር ምላሽ፣ ነፍሳችንን ለአንተ መስጠት አልቻልንምና፣ 'ክራ-ላይሶ'!  

አንተ የምሕረት አምላክ፣ 'ክራ-ላይሶ'!  አንተ የኛን በደልና ኃጢአት ተሸክመህ በመስቀል ላይ ሞተሃልና፣ 'ክራ-ላይሶ'! እንዲህ ያለ መውድድ፣ እንዲህ ያለ ፍቅር ለእኛ ለኃጢአተኞች አሳይተኻኛል፣ 'ክራ-ላይሶ'!

አንተ የፍቅር አምላክ፣ 'ክራ-ላይሶ'! የበደሉንና የጎዱንን ሁሉ ይቅር ማለት አቅቶናልና፣ 'ክራ-ላይሶ'! ወንድሞች በኅብረት መቀመጥ አቅቶናልና፣ 'ክራ-ላይሶ'! ነፍሳችንን ለአንተ አሳልፈን ከመስጠት ይልቅ ነፍሳችንን ወድደናታልና፣ 'ክራ-ላይሶ'! ራሳችንን ለአንተ አሳልፈን ከመስጠት ይልቅ፣ ራሳችንን ወድደናልና፣ ኪሪዬ ኤሊይሶን!

አቤቱ የፍቅርና የምሕረት ጌታ፣ ኪሪዬ ኤሊይሶን – ማረን አቤቱ ማረን!!
መጋቢያን፣ ሐዋርያት፣ ነቢያት፣ አስተማሪዎች፣ ወንጌላዊያን፣ ምዕመን አገልጋዩ ሁሉ ራስ ወዳዶች ሆነን ተገኝተናልና፣ 'ክራ-ላይሶ'! እርስ በርሳችን ከመዋደድ ይልቅ፣ እርስ በርሳችን በመገፋፋት አጥፍተናልና፣ 'ክራ-ላይሶ'! በምንሠራው ሥራ ለወንጌል እንቅፋት፣ ለመንጋው ስብራት ሆነናልና፣ 'ክራ-ላይሶ'!

አንዱ የሌላውን በር በመዝጋት፣ አንዳችን የሌላችን ራዕይ በማሰናከል በድለናልና፣ 'ክራ-ላይሶ'! በጥላቻ ሥራ እየተሠማራን፣ በጥላቻ መንገድ ገብተን እየሄድን እኛ ወድቀን ሌሎችን በመጣል አጥፍተናልና፣ 'ክራ-ላይሶ'!

'ክራ-ላይሶ'! የፍቅርና የምሕረት ጌታ፣ ኪሪዬ ኤሊይሶን – ማረኝ አቤቱ ፈጣሪ፣ እኔም አውቃለሁ በደሌን!!

ኪሪዬ ኤሊይሶን! ለሀ ሴንተማራይ!

ትምህርቱ ጠቅሞታል? እንግዲያውስ ላይክ ያድርጉ፡፡ ጌታ ይባርክዎ!

No comments:

Post a Comment