ዲቮሽ 231/07፥ ረቡዕ፥ ሚያዝያ 21/07 ዓ/ም
(በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)
ሚሊዮኖች ሲወድቁ - ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
(በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)
ሚሊዮኖች ሲወድቁ - ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
እግዚአብሔርም አለ፥ የሰዶምና የገሞራ ጩኸት እጅግ በዝቷልና፥ ኃጢአታቸውም እጅግ ከብዳለችና … በከተማዪቱ አስር ጻድቃን ባገኝ ሥፍራውን ሁሉ ስለ እነርሱ እምራለሁ … አላጠፋትም (ዘፍ 18፡20-33)
ከሰሞኑ በደረሰው ከባድ ርዕደ መሬት በኔፓል በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የማለቃቸውን ዜና ሰማን፡፡ ከሳምንታት በፊትም 30 ኢትዮጵያዊያን ክርስቲያኖች በእምነታቸው ምክንያት አንገታቸው ሲቀላ፥ የጥይት ናዳ እንደዝናብ ሲዘንብባቸው አየን፡፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ከዚህ ወቅት ትንሽ ቀደም ብሎም ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ፥ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ መጤ ዘጎች ከነሕይወታቸው ሲቃጠሉ ተመለከትን፡፡ ከዚህ ጥቂት ቀደም ብሎም፥ 21 ግብጻዊያን ክርስቲያኖች እንደ በግ ሲታረዱ አየን፡፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ከጥቂት ወራት በፊትም በሺዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያን ኩርዶች፥ ኢራቃዊያን፥ ሶሪያዊያን፥ ሊባኖሳዊያን፥ ፓክስታናዊያን፥ ሕንዳዊያንና ሌሎችም የአረብ ክርስቲያኖች ጅምላ ጭፍጨፋ ሲደርስባቸው አየን፥ ሰማንም፡፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ከዚህ ጥቂት ቀደም ብሎም በኬንያ፥ በናይጄሪያ፥ የሚዘገንኑ ጅምላ ጨራሽ ጭፍጨፋዎች መደረሳቸውን አየን፡፡ ከዚህ ቀድም ብሎም በፈረንሣይ፥ በአረብ ኢሚሬትስ ጅምላ ጭፍጨፋዎች ደርሰዋል፡፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ከዚህ በፊትም፥ በኢትዮጵያና ኤርትራ፥ በሶማሊያና ሱዳን፥ በኮንጎና ሩዋንዳ፥ በሌሎቹም ቦታዎች በሚሊዮችና በመቶ ሺዎች በሚቆጠሩ የሰው ልጆች ላይ እጅግ ዘግናኝ የሆኑ ጅምላ ጭፍጨፋዎች ሲደርሱ አይተናል፡፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ከዚህም ቀደም ብሎ፥ በኢትዮጵያ የደረሰው ቀይና ነጭ ሽብር፥ በየዘመኑም የሚከሰተው አረንጓዴ ቢጫ ሰማያዊ ችግር፥ የቅንጅት፥ የሌጣ፥ ሐይማኖታዊና የፖለቲካ ችግር የብዙ ሰው ሕይወት በከንቱ ተቀጥፏል፡፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ወገኖች ሆይ፥ በጠራራ ጸሐይ ይኼ ሁሉ አደጋ፥ ይኼ ሁሉ ጥፋት፥ ይኼ ሁሉ እልቂት በየቦታው ሲደርስ ጻድቃን ወዴት አሉ? በጨካኞች ካራ ሚሊዮኖች ሲቀሉ በጨካኞች ጥይት ሚሊዮኖች ሲወድቁ፥ ሚሊዮኖች ተስድደው፥ ሚሊዮኖች ተፈናቅለው፥ ሚሊዮኖች ሲጠፉ ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ወገኖች ሆይ፥ "አስር ጻድቃን ያሉበት ከተማ አትጠፋም" ከተባለ፥ ከተሞች ሲፈርሱ፥ ከተሞች ሲጠፉ ጻድቃን ወዴት አሉ? በከተማ ሽብር፥ በገጠሩ ሽብር፥ በሀገሩ ሽብር፥ በአህጉሩ ሽብር፥ በዓለማችን ሽብር ሲሆን ጻድቃን ወዴት አሉ? ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ? ወይስ፥ በየከተማው ያሉ የጻድቃኖቻችን ቁጥር አስርም አይሞላም?
ትምህርቱ ጥቅምዎት ከሆነ ላይክ ያድርጉ! ጌታ ይባርክዎ!
ከሰሞኑ በደረሰው ከባድ ርዕደ መሬት በኔፓል በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የማለቃቸውን ዜና ሰማን፡፡ ከሳምንታት በፊትም 30 ኢትዮጵያዊያን ክርስቲያኖች በእምነታቸው ምክንያት አንገታቸው ሲቀላ፥ የጥይት ናዳ እንደዝናብ ሲዘንብባቸው አየን፡፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ከዚህ ወቅት ትንሽ ቀደም ብሎም ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ፥ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ መጤ ዘጎች ከነሕይወታቸው ሲቃጠሉ ተመለከትን፡፡ ከዚህ ጥቂት ቀደም ብሎም፥ 21 ግብጻዊያን ክርስቲያኖች እንደ በግ ሲታረዱ አየን፡፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ከጥቂት ወራት በፊትም በሺዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያን ኩርዶች፥ ኢራቃዊያን፥ ሶሪያዊያን፥ ሊባኖሳዊያን፥ ፓክስታናዊያን፥ ሕንዳዊያንና ሌሎችም የአረብ ክርስቲያኖች ጅምላ ጭፍጨፋ ሲደርስባቸው አየን፥ ሰማንም፡፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ከዚህ ጥቂት ቀደም ብሎም በኬንያ፥ በናይጄሪያ፥ የሚዘገንኑ ጅምላ ጨራሽ ጭፍጨፋዎች መደረሳቸውን አየን፡፡ ከዚህ ቀድም ብሎም በፈረንሣይ፥ በአረብ ኢሚሬትስ ጅምላ ጭፍጨፋዎች ደርሰዋል፡፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ከዚህ በፊትም፥ በኢትዮጵያና ኤርትራ፥ በሶማሊያና ሱዳን፥ በኮንጎና ሩዋንዳ፥ በሌሎቹም ቦታዎች በሚሊዮችና በመቶ ሺዎች በሚቆጠሩ የሰው ልጆች ላይ እጅግ ዘግናኝ የሆኑ ጅምላ ጭፍጨፋዎች ሲደርሱ አይተናል፡፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ከዚህም ቀደም ብሎ፥ በኢትዮጵያ የደረሰው ቀይና ነጭ ሽብር፥ በየዘመኑም የሚከሰተው አረንጓዴ ቢጫ ሰማያዊ ችግር፥ የቅንጅት፥ የሌጣ፥ ሐይማኖታዊና የፖለቲካ ችግር የብዙ ሰው ሕይወት በከንቱ ተቀጥፏል፡፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ወገኖች ሆይ፥ በጠራራ ጸሐይ ይኼ ሁሉ አደጋ፥ ይኼ ሁሉ ጥፋት፥ ይኼ ሁሉ እልቂት በየቦታው ሲደርስ ጻድቃን ወዴት አሉ? በጨካኞች ካራ ሚሊዮኖች ሲቀሉ በጨካኞች ጥይት ሚሊዮኖች ሲወድቁ፥ ሚሊዮኖች ተስድደው፥ ሚሊዮኖች ተፈናቅለው፥ ሚሊዮኖች ሲጠፉ ጻድቃን ወዴት ሄዱ?
ወገኖች ሆይ፥ "አስር ጻድቃን ያሉበት ከተማ አትጠፋም" ከተባለ፥ ከተሞች ሲፈርሱ፥ ከተሞች ሲጠፉ ጻድቃን ወዴት አሉ? በከተማ ሽብር፥ በገጠሩ ሽብር፥ በሀገሩ ሽብር፥ በአህጉሩ ሽብር፥ በዓለማችን ሽብር ሲሆን ጻድቃን ወዴት አሉ? ይኼ ሁሉ ሲሆን ጻድቃን ወዴት ሄዱ? ወይስ፥ በየከተማው ያሉ የጻድቃኖቻችን ቁጥር አስርም አይሞላም?
ትምህርቱ ጥቅምዎት ከሆነ ላይክ ያድርጉ! ጌታ ይባርክዎ!
No comments:
Post a Comment