ዲቮሽን ቁጥር 157/07 ቅዳሜ
( በ ጌታሁን ሐለፎም )
እረፍት በማን ?
ለሰላም ሳነሳ ከረጅም ጊዜ በፊት ያየሁትን ስዕል አስታወስኩኝ :: በጣም በሚነዋወጥ ባህር ላይ አንዲት ወፍ በአንዲት ከባህሩ ስር በወጣች ቀጭን ሰንበሌጥ ላይ ያለስጋት ቁጭ ብላ ትታያለች ፣
የወጀቡ መናወጥ ለጉድ ነው ፣ እሷ ግን ድንጋጤም አይታይባትም ፣ ለመብረር ያሰበችም አትመስልም ፍጹም ተደላድላለች :: ትርኢቱ በሆነው ባልሆነው ለምንፈራ እና ለምንደነግጥ ለእኛ ያስቀናል ፣ ወይ መታደል ያስብላል:: ለመሆኑ በዚያ በሚያስፈራ እና በሚያስደነግጥ ወጀብ ወፏ ለምንድ ነው ፍርሃት ያልታየባት ለምንድን ነው ያልተሽበረችው ? ብለን ብንጠይቅ ፡ መልሱ ቀላል ነው ወፏ መብረር ስለምትችል የወጀቡ ግርግር ስጋት ሊፈጥርባት አይችልም ።
መቸስ የፃድቅ ሰው አይን በራሱ ላይ ነው። ይላል እና ቃሉ ፡ እራሴን አየሁ ፡ ቅዱሳን ወገኖቼን አሰብኩ ፡ ለምንድነው የምንናወጠው ? በሆነው ባልሆነው ለምንድን ነው ልባችን የሚርደው ? የጌታ ጥበቃ የት ሄዶ ?
በዚህች ትንሽ ፍጥረት አይምሮ ውስጥ መብረር መቻሏ ታላቅ ድፍረት በውስጧ እንዲፈጠር አድርጓታል ፣ በቃ አትደነግጥም ። ይህንን ጥበብ ማን ሰጣት ይህንን ተፈጥሮ ማን አደላት ? ጌታ ።
አሁን ያለንበትን ዘመን ስናይ ከመቸውም በበለጠ ፣ ምድር በከፍተኛ የሰላም ማጣት ፣ ወጀብ እና ነውጥ ውስጥ እንደምትገኝ መረዳት ይቻላል ::ምንም እንኳ ሰላምን በምድር ዙሪያ ለማምጣት የተለያዩ ሙከራወች በተለያዪ ተቁዋሞች ቢካሄዱም፣ በጠረጴዛ ዙሪያ ሀያላኖች ቢመክሩም ፣ ከረጅም ዘመን በፊት የተቋቋሙ የመንግስታት ድርጅቶች የተነሱበትን አላማ ግብ ሳይመቱ እዚህ ደርሰዋል ።
እንዲያውም በምድር ላይ እንደዚህ ያለ የፍርሃት እና የሰቀቀን ድምፅ ታይቶ እና ተሰምቶ አይታወቅም ::
የዜና ማሰራጫወች በጎ እና ተስፋ ያለበትን ወሬ ማሰማት ከተው ቆይተዋል ። ሁሉም የሞት ወሬ ፣ የሽብር ዜና። ምክኒያቱም የአለም ገጽታ ተልለውጧል ፣ በየትኛውም ስፍራ የጦርነት ድባብ ነግሷል ምን ይደረግ ሰላምን የሚወክል ጠፋ ሰላምን የሚያመጣ ታጣ ::
የዜና ማሰራጫወች በጎ እና ተስፋ ያለበትን ወሬ ማሰማት ከተው ቆይተዋል ። ሁሉም የሞት ወሬ ፣ የሽብር ዜና። ምክኒያቱም የአለም ገጽታ ተልለውጧል ፣ በየትኛውም ስፍራ የጦርነት ድባብ ነግሷል ምን ይደረግ ሰላምን የሚወክል ጠፋ ሰላምን የሚያመጣ ታጣ ::
ሁሉ አሸባሪ ሁሉ ገዳይ ሆነ ::ዛሬ ማእበሉ እና ወጀብ በበዛበት በዚህ አስከፊ ዘመን እንደ ወፏ በጸጥታ ለማረፍ ሌላ አማራጭ የለም ፣ ከአንዱ ከሰላም አባት በስተቀር፣ ሌላ መፍትሄ አይገኝም እሱም እየሱስ ነው :።
የሰላምን መንገድ የሚያመላክት ሌላ መጽሃፍ አይገኝም :: ሰላም በክርስቶስ ካልሆነ በስተቀር ፈጽሞ አይታሰብም :: በዚህ ሰዓት እኔና እናንተ እንደወፏ በርጋታ እና ያለ ስጋት ልንቀመጥ ያስፈልገናል :: ንጉሱ ላይ ተደግፈን፡ሩጫችን የጌታ ነው ፡ ኑሮአችን የሱ ነው፡እኛ የራሳችን አይደለንም፡
ባለ ቤት አለን፡እሱ ደግሞ የሁሉ የበላይ ነው፡አስተማማኝ።
ባለ ቤት አለን፡እሱ ደግሞ የሁሉ የበላይ ነው፡አስተማማኝ።
በወጀብ ውስጥ እረፍት የሆነውን ጌታ አስረግጠን እንወቀው። ከሚደነግጠው ጋር አንደንግጥ ከሚፈራው ጋር አንፍራ :: በወጀብ እና ባውሎ ነፋስ መንገድ ባለው አምላክ እንታመን ።ወፍዋ በወጀብ ባውሎነፋስ እንዳትናወጥ የሚያስችል ተፈጥሮ ያላበሳት እግዚአብሔር ነው ።
እኛ ደግሞ ወፍዋ የሌላት ሰብእና አለን ። ክርስቶስ ወዶን ስለኛ ሞቶ ከዘላለም የሞት ፍርሀት ነፃ አውጥቶናል።ከጌታ የተነሳ ዋጋችን እጅግ ታላቅ ነው።
እኛ ደግሞ ወፍዋ የሌላት ሰብእና አለን ። ክርስቶስ ወዶን ስለኛ ሞቶ ከዘላለም የሞት ፍርሀት ነፃ አውጥቶናል።ከጌታ የተነሳ ዋጋችን እጅግ ታላቅ ነው።
ጌታም በ መዝ.(46) 10 ላየ ሲናገር እንዲህ ብሎአል ``ዕረፉ እኔም አምላክ እንደሆንኩ እወቁ ``
ይህ መልእክት ለሌሎች ይጠቅማል ብለው ካሰቡ ሼር በማድረግ የጌታን መንግስት ያገልግሉ።
No comments:
Post a Comment