Sunday, February 15, 2015

እረፍት በማን ?

ዲቮሽን ቁጥር 157/07 ቅዳሜ
( በ ጌታሁን ሐለፎም )

እረፍት በማን ?
ለሰላም ሳነሳ ከረጅም ጊዜ በፊት ያየሁትን ስዕል አስታወስኩኝ :: በጣም በሚነዋወጥ ባህር ላይ አንዲት ወፍ በአንዲት ከባህሩ ስር በወጣች ቀጭን ሰንበሌጥ ላይ ያለስጋት ቁጭ ብላ ትታያለች ፣
የወጀቡ መናወጥ ለጉድ ነው ፣ እሷ ግን ድንጋጤም አይታይባትም ፣ ለመብረር ያሰበችም አትመስልም ፍጹም ተደላድላለች :: ትርኢቱ በሆነው ባልሆነው ለምንፈራ እና ለምንደነግጥ ለእኛ ያስቀናል ፣ ወይ መታደል ያስብላል:: ለመሆኑ በዚያ በሚያስፈራ እና በሚያስደነግጥ ወጀብ ወፏ ለምንድ ነው ፍርሃት ያልታየባት ለምንድን ነው ያልተሽበረችው ? ብለን ብንጠይቅ ፡ መልሱ ቀላል ነው ወፏ መብረር ስለምትችል የወጀቡ ግርግር ስጋት ሊፈጥርባት አይችልም ።
መቸስ የፃድቅ ሰው አይን በራሱ ላይ ነው። ይላል እና ቃሉ ፡ እራሴን አየሁ ፡ ቅዱሳን ወገኖቼን አሰብኩ ፡ ለምንድነው የምንናወጠው ? በሆነው ባልሆነው ለምንድን ነው ልባችን የሚርደው ? የጌታ ጥበቃ የት ሄዶ ?
በዚህች ትንሽ ፍጥረት አይምሮ ውስጥ መብረር መቻሏ ታላቅ ድፍረት በውስጧ እንዲፈጠር አድርጓታል ፣ በቃ አትደነግጥም ። ይህንን ጥበብ ማን ሰጣት ይህንን ተፈጥሮ ማን አደላት ? ጌታ ።
አሁን ያለንበትን ዘመን ስናይ ከመቸውም በበለጠ ፣ ምድር በከፍተኛ የሰላም ማጣት ፣ ወጀብ እና ነውጥ ውስጥ እንደምትገኝ መረዳት ይቻላል ::ምንም እንኳ ሰላምን በምድር ዙሪያ ለማምጣት የተለያዩ ሙከራወች በተለያዪ ተቁዋሞች ቢካሄዱም፣ በጠረጴዛ ዙሪያ ሀያላኖች ቢመክሩም ፣ ከረጅም ዘመን በፊት የተቋቋሙ የመንግስታት ድርጅቶች የተነሱበትን አላማ ግብ ሳይመቱ እዚህ ደርሰዋል ።
እንዲያውም በምድር ላይ እንደዚህ ያለ የፍርሃት እና የሰቀቀን ድምፅ ታይቶ እና ተሰምቶ አይታወቅም ::
የዜና ማሰራጫወች በጎ እና ተስፋ ያለበትን ወሬ ማሰማት ከተው ቆይተዋል ። ሁሉም የሞት ወሬ ፣ የሽብር ዜና። ምክኒያቱም የአለም ገጽታ ተልለውጧል ፣ በየትኛውም ስፍራ የጦርነት ድባብ ነግሷል ምን ይደረግ ሰላምን የሚወክል ጠፋ ሰላምን የሚያመጣ ታጣ ::
ሁሉ አሸባሪ ሁሉ ገዳይ ሆነ ::ዛሬ ማእበሉ እና ወጀብ በበዛበት በዚህ አስከፊ ዘመን እንደ ወፏ በጸጥታ ለማረፍ ሌላ አማራጭ የለም ፣ ከአንዱ ከሰላም አባት በስተቀር፣ ሌላ መፍትሄ አይገኝም እሱም እየሱስ ነው :።
የሰላምን መንገድ የሚያመላክት ሌላ መጽሃፍ አይገኝም :: ሰላም በክርስቶስ ካልሆነ በስተቀር ፈጽሞ አይታሰብም :: በዚህ ሰዓት እኔና እናንተ እንደወፏ በርጋታ እና ያለ ስጋት ልንቀመጥ ያስፈልገናል :: ንጉሱ ላይ ተደግፈን፡ሩጫችን የጌታ ነው ፡ ኑሮአችን የሱ ነው፡እኛ የራሳችን አይደለንም፡
ባለ ቤት አለን፡እሱ ደግሞ የሁሉ የበላይ ነው፡አስተማማኝ።
በወጀብ ውስጥ እረፍት የሆነውን ጌታ አስረግጠን እንወቀው። ከሚደነግጠው ጋር አንደንግጥ ከሚፈራው ጋር አንፍራ :: በወጀብ እና ባውሎ ነፋስ መንገድ ባለው አምላክ እንታመን ።ወፍዋ በወጀብ ባውሎነፋስ እንዳትናወጥ የሚያስችል ተፈጥሮ ያላበሳት እግዚአብሔር ነው ።
እኛ ደግሞ ወፍዋ የሌላት ሰብእና አለን ። ክርስቶስ ወዶን ስለኛ ሞቶ ከዘላለም የሞት ፍርሀት ነፃ አውጥቶናል።ከጌታ የተነሳ ዋጋችን እጅግ ታላቅ ነው።
ጌታም በ መዝ.(46) 10 ላየ ሲናገር እንዲህ ብሎአል ``ዕረፉ እኔም አምላክ እንደሆንኩ እወቁ ``
ይህ መልእክት ለሌሎች ይጠቅማል ብለው ካሰቡ ሼር በማድረግ የጌታን መንግስት ያገልግሉ።

No comments:

Post a Comment