Thursday, January 29, 2015

ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ!

ዲቮሽን .141/07    ሐሙስ፣ ጥር 21/07 .. 
(
በመጋቢ ተስፋሁን ሐጢያ)



ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ!

እናንተ ደካሞች፥ ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ (ማቴ 1128)፡፡
አዋጅ፥ አዋጅ፥ አዋጅ! ዛሬ በልዩ ልዩ ሽክም ምክንያት እያለቀሱ ላሉ ሁሉ የሚሆን መልዕክት ነው የተቀበልኩት!
አዋጅ፥ አዋጅ፥ አዋጅ! በዛሬው ዕለት እንባቸው እየፈሰሰ ላለ፥ መንታ መንታ እንባዎች ፊታቸው ላይ እየጎረፈ ላለ፥ በእንባቸው ምክንያት ፊታቸው ለበለዘ፥ በእንባቸው ምክንያት አይናቸው ለፈዘዘ ሁሉ የሚሆን መልዕክት!
አዋጅ፥ አዋጅ፥ አዋጅ! ለሰው ሁሉ የሚሆን መልዕክት! አንገታቸውን ደፍተው፥ ፊታቸውን ቀብረው በሐፍረትና ጸጸት ለሚመላለሱ፥ ሸክም ከብዶባቸው ለሚንገዳገዱ ለእግዚአብሔር ልጆች የተላከ መልዕክት!

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፥ እናንተ ደካሞች፥ ሸክም የከበደባችሁ ሁሉ፥ ሽክማችሁን ስጡኝ! ሸክማችሁን ሁሉ፥ ወደ እኔ አምጡና በእግሬ ስር ጣሉ! ትልቅ ይሁን ትንሽ፥ ጥቂት ሆነ ብዙ፥ ጠባብ ሆነ ሰፊ፥ የስጋና የነፍስ ማናቸውንም ሸክም ለእኔ ስጡኝና እስኪ ላሳርፋችሁ!

No comments:

Post a Comment