Wednesday, December 10, 2014

የጴንጠቆስጤነት አቡጊዳ(#10) –የነፍሳት ምርኮ!

ዲቮሽን ቁ.90/07     ማክሰኞ፣ ሕዳር 30/07 ዓ.ም.
(በመጋቢ ተስፋሁን ሐጢያ)

የጴንጠቆስጤነት አቡጊዳ(#10) –የነፍሳት ምርኮ!

እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ በሕዝብ ሁሉ ፊት ሞገስ ነበራቸው። ጌታም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር።(የሐዋ 2፡47)።

ወገኖች ሆይ፣ መንፈስ ቅዱስ በሙላት በሚሠራበት ቦታ ሁሉ አዳዲስ ነፍሳት ይጨመራሉ፡፡ ይህ የታላቁ ተልዕኳችን ቁልፍ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱና ዋናው ነው፡፡ ሺህ ጊዜ ሺህ ሪቫይቫልና ተአምራት ቢኖር፣ እልፍ ጊዜ እልፍ ድንቅና ምልክት ቢኖር፣ ነገር ግን ሰዎች ካልዳኑ ዋጋ የለውም!

ወገኖች ሆይ፣ ጴንጠቆስጤነት ያለ ነፍሳት መዳን፣ ያለ አባላት መጨመር ሊታሰብ አይችልም፡፡ ሺህ ጊዜ ሺህ ስብከት፣ እልፍ ጊዜ እልፍ ትምህርት ቢኖር ነገር ግን ሰዎች ካልዳኑ ምንም ዋጋ የለውም! ነፍሳት የማያድን ስብከት፣ ሕይወት የማያድን ትምህርት የምግብ ፍርፋሪ፣ የእህል ገለባ ነው!

ታውቃላችሁ፣ የጴንጠቆስጤነት አንዱ መገለጫ፣ የነፍሳቶች መዳን፣ የሰዎች መትረፍ ነው! ሰዎች ካላዳንን ታላቁ ተልዕኮ፣ የስማ በለው ወሬ፣ የተረት ተረት ነው!

ታውቃላችሁ፣ ነፍሳት ካላዳንን፣ ታላቁ ተልዕኮ የወረቀት ጽሁፍ፣ ባዶ መፈክር ነው፡፡ ነፍሳት ካላዳንን የውሃ ጥምቀቱ፣ የጌታ እራቱ፣ ደቀመዝሙርነቱ፣ የሰሚ ሰሚ ነው፡፡

ታውቃላችሁ፣ ሺህ ጊዜ ሺህ ልሳን፣ እልፍ ጊዜ እልፍ ትንቢት፣ ነፍሳት ካላዳነ የከንቱ ከንቱ ነው! ሺህ ጊዜ ሺህ ጸጋ፣ እልፍ ጊዜ እልፍ ቅባት ነፍሳት ካላዳነ የከንቱ ከንቱ ነው!

ታውቃላችሁ፣ ሺህ ጊዜ ሺህ ጴንጠቆስጤነት፣ እልፍ ጊዜ እልፍ የእምነት ተከታይነት ነፍሳት ካላዳነ የከንቱ ከንቱ ነው! የኛ ፓስተርነት፣ የኛ ነቢይነት፣ የኛ ሐዋርያነት፣ የኛ ዘማሪነት፣ የኛ ወንጌላዊነት፣ ነፍሳት ካላዳነ የከንቱ ከንቱ ነው! (ተፈጸመ)

-------------------------
6 ማስታወቂያዎች፣

(1) የወንጌላዊው እጮኛ መጽሐፍ፣ እሁድ ታህሳስ 12 ቀን ከቀኑ በ10፡00 ካዛንቺስ በሚገኘው ፔንቴኮስታል ቴኦሎጂካል ኮሌጅ አዳራሽ ይመረቃል፡፡ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል፡፡

(2) ከዚህ በፊት ለአምስት የፌስቡክ ተከታታዮቼ ስጦታ እንደምሰጥ ቃል ገብቼ ነበር፡፡ በመሆኑም፣ እነዚህ አምስቱ ከቻሉ በመጽሐፉ ምርቃ ቀን ተገኝተው የዚህን ልብ አንጠልጣይ መጽሐፍ አንዳንድ ነጻ ኮፒ በሕዝብ ፊት እነዲወስዱ እጋብዛለሁ፡፡ የማግይገኙም ቢሆን ተወካይ እንዲልኩ በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡

(3) ከመስከረም 1/2007 ጀምሮ እስከዛሬ ሕዳር 30/2007 ድረስ በነበሩት 90 ቀናት፣ ጌታ ረድቶኝ 90 ዕለታዊ ዲቮሽኖች በፌስቡክና በብሎግ ፖስት በማድረግ አገልግያለሁ፡፡ በቀጣየቹ ሶስት ወራት ደግሞ ከዚህ በተሻለ እንዳገለግላችሁ ምክራችሁና መልካም አስተያየታችሁ እንዳይለየኝ በጌታ ፍቅር እጠይቃለሁ፡፡

(4) ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ የወጡ 90 የዲቮሽን ትምህርቶች በአንድ ላይ ተሰብስበውና በመጽሐፍ ታትመው እንደጌታ ፈቃድ በቅርቡ ለአንባቢያን ይደርሳሉ፡፡ ጌታ የተመሰገነ ይሁን፡፡

(5) በቁጥር 4 በተገለጸው የዲቮሽን መጽሐፍ ላይ የ90 ቀን ዲቮሽኖቹን በየዕለቱ በመከታተልና ላይክና ሼር በማድረግ ተግቶ በማገልገል ብልጫ ላሳዩ ሶስት ሰዎች ይህ መጽሐፍ የሕይወት ዘመን ስጦታ እንዲሆንላቸውና ለስማቸውም ቋሚ መታሰቢያ ሆኖ እንዲታተም ወስኛለሁ፡፡ በመሆኑም፣ የእነዚህን ሰዎች ማንነት በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ይፋ የማደርግ መሆኑን ከወዲሁ አሳውቃለሁ፡፡

(6) ጌታ ቢፈቅድ ለሚቀጥሉትም ጊዜያት ዲቮሽኖቹን በየዕለቱ በመከታተልና ላይክና ሼር በማድረግ ተግቶ በማገልገል ብልጫ ለሚያሳዩ ሌሎች ወገኖችም እንዲሁ የሕይወት ዘመን ስጦታ እንዲሆንላቸውና መጽሐፎቹን በመታሰቢያነት አሳትማለሁ፡፡

ለበለጠ ማብራሪያ በሞባይል +251-911-678158 ይደውሉ፡፡


ጌታ ይባርካችሁ፡፡ ሁላችሁንም እወዳችኋለሁ፡፡

No comments:

Post a Comment