Monday, December 29, 2014

የሙሉጊዜ አገልጋዮች ክፍያ – በኢትዮጵያ! 2

ዲቮሽን .110/07 ሰኞ፣ ታህሳስ 20/07 ..
(በመጋቢ ተስፋሁን ሐጢያ)


ሙሉጊዜ አገልጋዮች ክፍያ – በኢትዮጵያ! 2

ነገር ግን አሁን ከጊዜ በኋላ ስለ እኔ እንደ ገና ልታስቡ ስለ ጀመራችሁ፥ በጌታ እጅግ ደስ ይለኛል፤ ጊዜ አጣችሁ እንጂ፥ ማሰብስ ታስቡ ነበር።የፊልጵስዩስ ሰዎች ሆይ፥ ወንጌል በመጀመሪያ ሲሰበክ፥ ከመቄዶንያ በወጣሁ ጊዜ፥ ከእናንተ ብቻ በቀር ሌላ ቤተ ክርስቲያን በመስጠትና በመቀበል ስሌት ከእኔ ጋር እንዳልተካፈለች እናንተ ደግሞ ታውቃላችሁ (ፊል 410-15)

«አንድ ጊዜ አንድ የሙሉ ጊዜ አገልጋይ ለወራት ያህል ይታመምና ምንም አይነት የሕክምና ዕርዳታ ሳያገኝ አልጋ ላይ ይወድቃል፡፡ አገልጋዩ ቤተሰብና የቅርብ የሆነ ዘመዱ የማይኖርበት አካባቢ ይኖር ስለነበረ የጤንነት ሁኔታው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተዳከመ መጣ፡፡ በሚያገለግልበት አጥቢያ ውስጥ በወንጌል አገልግሎት ስራ ላይ የተሠማራ ከእርሱ ሌላ ረዳት ባለመኖሩ የቤተክርስቲያን መሪዎችን ያሳስብ ጀመር፡፡ ነገር ግን ስለወንጌላዊው ሕመምና ለወራት በአልጋ ላይ የመውደቁ ነገር ያሳሰበው፣ ቀርቦ የጠየቀውም ሆነ ዕርዳታ ያደረገለት አካል አልነበረም፡፡>>

<<አገልጋዩ ሕክምና ባለማግኘቱ ጤናው እየተቃወሰ ሄደ፡፡ በአጥቢያው ብቸኛ የነበረው አገልጋይ ለወራት ታምሞ አገልግሎት ሳይሰጥ የመቅረቱ ጉዳይ ያሳሰባቸው የቤተክርስቲያን መሪዎችን በቦታው ሌላ አገልጋይ አሰማሩ፡፡ መሪዎቹ ቀደም ሲል ለታማሚው አገልጋይ ይሰፍሩለት የነበረው ቀለብ በከፊል ተቀንሶ ይሰጠው ጀመር፡፡ ይህ ክፍያ ከቤት ኪራዩ ውጭ ለምንም የማይተርፍ ነበር፡፡>>

<<ለአገልጋዩ ቤት ያከራዩ የቤት ባለቤቶች <የዘመኑ በሽታ ሊሆን ይችላል> ብለው በመፍራት ቤታቸውን ለቅቆ እንዲወጣ ጠየቁት፡፡ ወንጌላዊውም ለጊዜው ሕመም ላይ ስላለ ቤት አፈላልጎ እስከሚወጣ ድረስ እንዲታገሱት ለመናቸው፡፡ በእነዚህ ጊዜያት ሁሉ ከቤተክርስቲያን አባላት የጠየቀው የለም፡፡>>

<<በመካከሉ አንድ ነገር ተፈጠረ፡፡ አገልጋዩ እንደ ወትሮው ቤት ሲከፍትና ሲዘጋ ለቀናት ያህል ያላዩት አከራዮቹ፣ የአገልጋዩን ቤት ቢያንኳኩ ከወደ ውስጥ <እነሆኝ> የሚል ድምጽ ይጠፋል፡፡ ጉዳዩ አብከንክኗቸው በሩን ጠጋ ብለው ሲመረምሩት መልካም ያልሆነ ጠረን  ይሸታቸው ይጀምራል፡፡>>

<<በሁኔታው የተደናገጡት የቤቱ አከራዮች ለፖሊስ ቢያመለክቱ ያላሰቡት አደጋ በቤታቸው ውስጥ ተከስቶ ያገኙታል፡፡ በተፋፈነና እጅግ በጣም በቆሸሸ ቤት ውስጥ ይኖር የነበረው አገልጋይ የምድር ሩጫውን አጠናቅቆ በሰላም ሲያገለግለው ወደነበረው አምላኩ ከሄደ ቀናት አልፈዋል፡፡>>

<<አዎ፣ እዚያ ረሀብ የለም፡፡ በሽታና ደዌ አይገኝበትም፡፡ በተፋፈነ ቤት መኖር የለም፡፡ የቤት ኪራይ አይከፈልበትም፡፡ በዚያ የሰው አይን ያላየው፣ ጆሮም ያልሰማው፣ እጅ ያልዳሰሰው፣ ነገር ግን እግዚአብሔር ለምርጦቹ ያዘጋጀው... >>

--------------------------------
‹‹የወንጌላዊ እጮኛ›› በሺዎች የተደነቀ ልብ አንጠልጣይ መጽሐፍ ትናንት፣ እሁድ፣ ታህሳስ 19 ቀን 2007 .. ከቀኑ 900 ተመርቋል፡፡


No comments:

Post a Comment