Tuesday, November 18, 2014

የእምነቴ መግለጫ

ዲቮሽን ቁ.69/07     ማክሰኞ፣ ሕዳር 9/07 ዓ.ም.
(በመጋቢ ተስፋሁን ሐጢያ)

የእምነቴ መግለጫ

እኔ፣ ሁሉን በሚችል፣ ሰማይንና ምድርን በፈጠረ በእግዚአብሔር አብ አምናለሁ፡፡

ደግምም በአንድ ልጁ፣ በመንፈስ ቅዱስ በተጸነሰ፣ በጴንጠናዊው በጲላጦስ ዘመን መከራን በተቀበለ፣ በተሰቀለ፣ በሞተ፣ በሶስተኛው ቀን ከሙታን በተነሳ፣ ወደ ሰማይ በወጣ፣ በእግዚአብሔር አብ ቀኝ በተቀመጠ፣ በሕያዋንና በሙታን ሊፈርድ ከዚያም በሚመለስ፣ በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምናለሁ፡፡

ደግሞም፣ በአንዲት ቅድስት በሐዋርያት ተክርስቲያን፣ በቅዱሳን አንድነት፣ በሥጋ ትንሳኤ፣ በዘላለም ሕይወት አምናለሁ፡፡

ደግሞም ከድኅነት በኋላ በሚሆን በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት፣ በልሳን መናገር፣ ዛሬም በሚሠራ በጸጋ ስጦታ፣ በሐዋርያት፣ በነቢያት፣ በድንቅና ተአምራት፣ በአጋንንት ማውጣት አምናለሁ፡፡


ደግሞም፣ በመጽሐፍ ቅዱስ፣ በቃሉ መገለጥ፣ በወቅታዊ ምሪት፣ በተቀባ ስብከት፣ በጸሎት፣ በመንፈስ መሞላት፣ አምናለሁ፡፡ አሜን፡፡

No comments:

Post a Comment