Monday, March 30, 2015

ማስታወሻ – ለእግዚአብሔር!





ዲቮሽን . 201/07 ሰኞ፥ መጋቢት 21/07 ..
(
በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)


ማስታወሻ – ለእግዚአብሔር!

12 ወራት፣ 52 ሣምንታት፣ 365 ቀናት፣ 8,760 ሰዓታት፣ 525,600 ደቂቃዎች፣ 31,536,000 ሰኮንዶች – ድፍን አንድ ዓመት – በታላቅ ምሕረትህና በርኅራኄህ አለፉ! 

አምላኬ ሆይ፣ በወንዞች ውስጥ ባለፍሁ ጊዜ አላሰጠሙኝም! በእሳትም ውስጥ በሄድሁ ጊዜ አላቃጠሉኝም፥ ነበልባሉም አልፈጀኝም! ውኆች ሲናወጡ፣ ማዕበሉ ሲቆጣ፣ በወጀብ በአውሎንፋስ አልተለየኸኝምና አመሰግንሃለሁ!

12 ወራት፣ 52 ሣምንታት፣ 365 ቀናት፣ 8,760 ሰዓታት፣ 525,600 ደቂቃዎች፣ 31,536,000 ሰኮንዶች – ድፍን አንድ ዓመት – መገሰጹንስ እጅግ ብትገስጸኝም፣ ነገር ግን ለሞት አሳልፈህ አልሰጠኸኝምና በጨመርኽልኝ ዕድሜ አገለግልሃለሁ!

አምላኬ ሆይ፣ ተርፌ በሕይወት እኖራለሁ እንጂ አልሞትም፤ የአንተንም ሥራ ገና እናገራለሁ! ከአዳኝ ወጥመድ፣ ከሚያስደነግጥ ነገር፣ ከአደጋ ከመቅሰፍት፣ ከሸማቂ ጠላት፣ ከድንገተኛ ጥፋት፣ አድነኸኛልና አመሰግንሃለሁ! 

አልሞትም በሕይወት እኖራለሁ እንጂ፥ የእግዚአብሔርንም ሥራ እናገራለሁ። መገሠጽስ እግዚአብሔር ገሠጸኝ ለሞት ግን አልሰጠኝም (መዝ 118፡17-18)።







No comments:

Post a Comment