ዲቮሽን ቁ. 201/07፣ ሰኞ፥ መጋቢት 21/07 ዓ.ም.
(በፓ/ር ተስፋሁን ሐጢያ)
ማስታወሻ
– ለእግዚአብሔር!
12 ወራት፣ 52 ሣምንታት፣ 365 ቀናት፣ 8,760 ሰዓታት፣ 525,600 ደቂቃዎች፣ 31,536,000 ሰኮንዶች – ድፍን አንድ ዓመት – በታላቅ ምሕረትህና በርኅራኄህ አለፉ!
አምላኬ ሆይ፣ በወንዞች ውስጥ
ባለፍሁ ጊዜ አላሰጠሙኝም! በእሳትም ውስጥ በሄድሁ ጊዜ አላቃጠሉኝም፥ ነበልባሉም አልፈጀኝም! ውኆች ሲናወጡ፣ ማዕበሉ ሲቆጣ፣ በወጀብ
በአውሎንፋስ አልተለየኸኝምና አመሰግንሃለሁ!
12 ወራት፣ 52 ሣምንታት፣ 365 ቀናት፣ 8,760 ሰዓታት፣ 525,600 ደቂቃዎች፣ 31,536,000 ሰኮንዶች – ድፍን አንድ ዓመት – መገሰጹንስ እጅግ ብትገስጸኝም፣ ነገር ግን
ለሞት አሳልፈህ አልሰጠኸኝምና በጨመርኽልኝ
ዕድሜ አገለግልሃለሁ!
አምላኬ ሆይ፣ ተርፌ በሕይወት እኖራለሁ እንጂ አልሞትም፤ የአንተንም ሥራ ገና እናገራለሁ! ከአዳኝ ወጥመድ፣ ከሚያስደነግጥ ነገር፣ ከአደጋ ከመቅሰፍት፣
ከሸማቂ ጠላት፣ ከድንገተኛ ጥፋት፣ አድነኸኛልና
አመሰግንሃለሁ!
አልሞትም በሕይወት እኖራለሁ እንጂ፥ የእግዚአብሔርንም ሥራ እናገራለሁ። መገሠጽስ እግዚአብሔር ገሠጸኝ ለሞት ግን አልሰጠኝም (መዝ 118፡17-18)።
| |
Welcome to my blog. You will find Bible based, Spirit filled, Christ Centered articles in Amharic and in English. The main purpose of these articles is Uplifting People. I am not a member of any political party. However, whenever I have a say, as a citizen, I do not hesitate to post my messages with a positive tone.
Monday, March 30, 2015
ማስታወሻ – ለእግዚአብሔር!
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment